ሚክያስ 1 – NASV & NUB

New Amharic Standard Version

ሚክያስ 1:1-16

1በይሁዳ ነገሥታት በኢዮአታም፣ በአካዝና በሕዝቅያስ ዘመን ወደ ሞሬታዊው ወደ ሚክያስ የመጣው የእግዚአብሔር ቃል፣ ስለ ሰማርያና ስለ ኢየሩሳሌም ያየው ራእይ ይህ ነው፤

2እናንተ አሕዛብ ሆይ፤ ሁላችሁም ስሙ፤

ምድር ሆይ፤ በውስጧም የምትኖሩ ሁሉ አድምጡ፤

ጌታ ከቅዱስ መቅደሱ፣

ልዑል እግዚአብሔር በእናንተ ላይ ይመሰክርባችኋል።

በሰማርያና በኢየሩሳሌም ላይ የተላለፈ ፍርድ

3እነሆ፤ እግዚአብሔር ከመኖሪያ ስፍራው ይመጣል፤

ወርዶም በምድር ከፍታዎች ላይ ይራመዳል።

4ተራሮች ከሥሩ ይቀልጣሉ፤

ሸለቆዎችም ይሰነጠቃሉ፤

በእሳት ፊት እንዳለ ሰም፣

በገደል ላይ እንደሚወርድ ፈሳሽ ይሆናሉ።

5ይህ ሁሉ የሚሆነው ስለ ያዕቆብ በደል፣

ስለ እስራኤልም ቤት ኀጢአት ነው።

የያዕቆብ በደል ምንድን ነው?

ሰማርያ አይደለችምን?

የይሁዳስ የኰረብታ መስገጃ ምንድን ነው?

ኢየሩሳሌም አይደለችምን?

6“ስለዚህ ሰማርያን የፍርስራሽ ክምር፣

ወይን የሚተከልባትም ስፍራ አደርጋታለሁ፤

ድንጋዮቿን ወደ ሸለቆ አወርዳለሁ፤

መሠረቷንም ባዶ አደርጋለሁ።

7ጣዖቶቿ ሁሉ ይሰባበራሉ፤

ለቤተ መቅደሷ የቀረበው ገጸ በረከት በእሳት ይቃጠላል፤

ምስሎቿን ሁሉ እደመስሳለሁ፤

ገጸ በረከቷን በዝሙት ዐዳሪነት እንደ ሰበሰበች ሁሉ፣

አሁንም ገጸ በረከቷ የዝሙት ዐዳሪነት ዋጋ መቀበያ ይሆናል።”

ልቅሶና ሐዘን

8በዚህ ምክንያት አለቅሳለሁ፤ ዋይ ዋይም እላለሁ፤

ባዶ እግሬንና ዕርቃኔን እሄዳለሁ፤

እንደ ቀበሮ አላዝናለሁ፤

እንደ ጕጕትም አቃስታለሁ።

9ቍስሏ የማይሽር ነውና፤

ለይሁዳ ተርፏል፤

እስከ ሕዝቤ መግቢያ በር፣

እስከ ኢየሩሳሌም እንኳ ደርሷል።

10በጌት1፥10 ጌት የሚለው ቃል በዕብራይስጡ አውራ ከሚለው ጋር ተመሳሳይ አነባበብ አለው። አታውሩት፤

ከቶም አታልቅሱ1፥10 ዕብራይስጡ ከዚህ ጋር ሲስማማ፣ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም ግን በአኮ ላይ አታልቅሱ ይላል። በአኮ የሚለው የዕብራይስጡ ቃል አለቀሰ ከሚለው የዕብራይስጡ ቃል ጋር ተመሳሳይ አነባበብ አለው።

በቤትዓፍራ1፥10 ቤትዓፍራ ትርጕሙ የትቢያ ቤት ማለት ነው።

በትቢያ ላይ ተንከባለሉ።

11እናንት በሻፊር1፥11 ሻፊር ትርጕሙ አስደሳች ማለት ነው። የምትኖሩ፣

ዕርቃናችሁን ሆናችሁ በኀፍረት ዕለፉ፤

በጸዓናን1፥11 ጸዓናን የሚለው ቃል በዕብራይስጡ ውጣ ከሚለው ጋር ተመሳሳይ አነባበብ አለው። የሚኖሩ

ከዚያ አይወጡም፤

ቤትዔጼል በሐዘን ላይ ናት፤

ለእናንተም መጠጊያ ልትሆን አትችልም።

12ከመከራው መገላገልን በመሻት፣

በማሮት1፥12 ማሮት የሚለው ቃል በዕብራይስጡ መራራ ከሚለው ጋር ተመሳሳይ አነባበብ አለው። የሚኖሩ በሥቃይ

ይወራጫሉ፤

እስከ ኢየሩሳሌም በር ሳይቀር፣

ክፉ ነገር ከእግዚአብሔር ዘንድ መጥቷልና።

13እናንት በለኪሶ1፥13 ለኪሶ የሚለው ቃል በዕብራይስጡ ቡድን ከሚለው ጋር ተመሳሳይ አነባበብ አለው። የምትኖሩ፣

ፈረሶችን ከሠረገላው ጋር አያይዙ፤

ለጽዮን ሴት ልጅ፣

የኀጢአት መጀመሪያ እናንት ነበራችሁ፤

የእስራኤል በደል

በእናንተ ዘንድ ተገኝቷልና።

14ስለዚህ እናንተ ለሞሬሼትጌት፣

ማጫ ትሰጣላችሁ፤

የአክዚብ1፥14 አክዚብ ትርጕሙ አታላይ ወይም ማታለል ማለት ነው። ከተማ፣

ለእስራኤል ነገሥታት መታለያ ትሆናለች።

15እናንት በመሪሳ1፥15 መሪሳ የሚለው ቃል በዕብራይስጡ ድል አድራጊ ከሚለው ጋር ተመሳሳይ አነባበብ አለው። የምትኖሩ

ድል አድራጊ አመጣባችኋለሁ፤

ያ የእስራኤል ክብር የሆነው

ወደ ዓዶላም ይመጣል።

16ደስ ለምትሰኙባቸው ልጆቻችሁ፣

በሐዘን ራሳችሁን ተላጩ፤

ራሳችሁን እንደ አሞራ ራስ ተመለጡት፤

ከእናንተ በምርኮ ይወሰዳሉና።

Swedish Contemporary Bible

Mika 1:1-16

Domsord över Juda och Israel

(1:2—3:12)

1Detta är Herrens ord som kom till Mika från Moreshet under de judiska kungarna Jotams, Achas och Hiskias regeringar, vad han fick se angående Samaria och Jerusalem.

2Hör, alla folk,

lyssna, du jord

och allt som finns där!

Herren, Herren, vittnar mot er,

Herren från sitt heliga tempel.

Dom över Samaria och Jerusalem

3Se! Herren kommer!

Han stiger ner från sin boning

och träder fram över jordens höjder.

4Bergen smälter under honom

och dalarna spricker upp,

som vax för elden

och som vatten störtar utför branten.

5Allt detta är för Jakobs överträdelse

och israeliternas synd.

Vad är Jakobs överträdelse?

Är det inte Samaria?

Vad är Judas offerplatser1:5 Enligt bl.a. Septuaginta synd.?

Är de inte Jerusalem?

6”Därför ska jag göra Samaria

till en stenhög på en åker,

till en plats där vingårdar kan planteras.

Jag ska vräka ner hennes stenar i dalen

och blotta hennes grundvalar.

7Alla hennes gudabilder

ska slås i stycken,

allt som hon tjänat som prostituerad

ska eldas upp,

och alla hennes avgudar

ska jag förgöra.

Med lönen för prostitution har hon skaffat dem,

och lön för prostitution ska de åter bli.”

Gråt och klagan

8Över detta gråter och klagar jag.

Jag går barfota och naken,

ylar som en schakal,

klagar som en berguv.

9Hennes sår kan inte läkas.

Det har kommit till Juda

och nått till mitt folks port,

till Jerusalem.

10Tala inte om det i Gat,

gråt inte!

Vältra er i stoftet

i Bet Leafra!1:10 Grundtexten innehåller mycket ordlek som inte låter sig översättas, och mycket av innebörden i detta avsnitt är osäkert. För v. 10f. jfr 2 Sam 1:20.

11Dra bort, Shafirs invånare,

i nakenhet och skam.

De som bor i Saanan

kan inte komma undan.

I Bet Haesel sörjer man,

dess beskydd har tagits ifrån er.

12Marots invånare vrider sig av smärta

och hoppas på något bättre,

för det onda som kommer från Herren

har nått Jerusalems portar.

13Spänn för stridsvagnar,

befolkningen i Lakish.

Det var början till dotter Sions synd

att man hos dig fann Israels överträdelser.

14Därför ska ni ge avskedsgåvor åt Moreshet Gat.

Husen i Aksiv har lurat kungarna i Israel.

15Jag ska åter låta erövrare komma mot er,

Mareshas invånare.

Israels härlighet ska komma

till Adullam.

16Raka ditt huvud och skär av ditt hår

för dina barns skull som var din glädje.

Gör dig skallig som gamen,

för de har förts bort från dig.