መዝሙር 99 – NASV & NSP

New Amharic Standard Version

መዝሙር 99:1-9

መዝሙር 99

ጻድቅና ቅዱስ አምላክ

1እግዚአብሔር ነገሠ፤

ሕዝቦች ይንቀጥቀጡ፤

በኪሩቤል ላይ በዙፋን ተቀምጧል፤

ምድር ትናወጥ።

2እግዚአብሔር በጽዮን ታላቅ ነው፤

ከሕዝቦችም ሁሉ በላይ ከፍ ከፍ ብሏል።

3ታላቁንና አስፈሪውን ስምህን ይወድሱ፤

እርሱ ቅዱስ ነው።

4ፍትሕን የምትወድድ፣ ኀያል ንጉሥ ሆይ፤

አንተ ትክክለኝነትን መሠረትህ፤

ፍትሕንና ቅንነትንም፣

ለያዕቆብ አደረግህ።

5አምላካችንን እግዚአብሔርን ከፍ ከፍ አድርጉት፤

በእግሩ መርገጫ ስገዱ፤

እርሱ ቅዱስ ነውና።

6ሙሴና አሮን ካህናቱ ከሆኑት መካከል ነበሩ፤

ሳሙኤልም ስሙን ከጠሩት መካከል አንዱ ነበረ፤

እነርሱ ወደ እግዚአብሔር ተጣሩ፤

እርሱም መለሰላቸው።

7ከደመና ዐምድ ውስጥ ተናገራቸው፤

እነርሱም ሥርዐቱንና የሰጣቸውን ድንጋጌ ጠበቁ።

8እግዚአብሔር አምላካችን ሆይ፤

አንተ መለስህላቸው፤

ጥፋታቸውን99፥8 ወይም የተፈጸመባቸውን በደል ማለት ነው። ብትበቀልም እንኳ፣

አንተ ይቅር የምትላቸው አምላክ ነህ።

9አምላካችንን እግዚአብሔርን ከፍ ከፍ አድርጉት፤

በቅዱስ ተራራውም ላይ ስገዱ፤

አምላካችን እግዚአብሔር ቅዱስ ነውና።

New Serbian Translation

Псалми 99:1-9

Псалам 99

1Господ влада –

нек народи дрхте!

Над херувимима он седи –

нек се земља тресе!

2Велики је Господ на Сиону,

узвишен је над свим народима.

3Велико ти име нека славе,

јер је страшно –

он је свет!

4Моћан је цар који воли правду;

Јакову си учврстио подједнако

и правду и праведност,

ти си то учинио.

5Уздижите Господа, Бога нашег!

Поклоните се пред подножјем његових ногу,

јер је он свет.

6Мојсије и Арон, свештеници његови;

Самуило, један од оних што су му се молили,

звали су Господа

и он их је услишио.

7У стубу од облака им је говорио,

а они су држали прописе

и уредбе које им је дао.

8О, Господе, Боже наш,

ти си их услишио!

Био си им Бог који опрашта

али и онај што кажњава њихова злодела.

9Уздижите Господа, Бога нашег!

Поклоните се на његовој светој гори,

јер наш Господ, Бог је свети.