መዝሙር 99 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 99:1-9

መዝሙር 99

ጻድቅና ቅዱስ አምላክ

1እግዚአብሔር ነገሠ፤

ሕዝቦች ይንቀጥቀጡ፤

በኪሩቤል ላይ በዙፋን ተቀምጧል፤

ምድር ትናወጥ።

2እግዚአብሔር በጽዮን ታላቅ ነው፤

ከሕዝቦችም ሁሉ በላይ ከፍ ከፍ ብሏል።

3ታላቁንና አስፈሪውን ስምህን ይወድሱ፤

እርሱ ቅዱስ ነው።

4ፍትሕን የምትወድድ፣ ኀያል ንጉሥ ሆይ፤

አንተ ትክክለኝነትን መሠረትህ፤

ፍትሕንና ቅንነትንም፣

ለያዕቆብ አደረግህ።

5አምላካችንን እግዚአብሔርን ከፍ ከፍ አድርጉት፤

በእግሩ መርገጫ ስገዱ፤

እርሱ ቅዱስ ነውና።

6ሙሴና አሮን ካህናቱ ከሆኑት መካከል ነበሩ፤

ሳሙኤልም ስሙን ከጠሩት መካከል አንዱ ነበረ፤

እነርሱ ወደ እግዚአብሔር ተጣሩ፤

እርሱም መለሰላቸው።

7ከደመና ዐምድ ውስጥ ተናገራቸው፤

እነርሱም ሥርዐቱንና የሰጣቸውን ድንጋጌ ጠበቁ።

8እግዚአብሔር አምላካችን ሆይ፤

አንተ መለስህላቸው፤

ጥፋታቸውን99፥8 ወይም የተፈጸመባቸውን በደል ማለት ነው። ብትበቀልም እንኳ፣

አንተ ይቅር የምትላቸው አምላክ ነህ።

9አምላካችንን እግዚአብሔርን ከፍ ከፍ አድርጉት፤

በቅዱስ ተራራውም ላይ ስገዱ፤

አምላካችን እግዚአብሔር ቅዱስ ነውና።

Japanese Contemporary Bible

詩篇 99:1-9

99

1全世界の王、主は、

ケルビムの上の王座に

ついておられます。

諸国民は震え上がり、大地は揺らぎますように。

2シオンに立たれる主のご威光は、

この世の支配者たちには、はるかに及ばないものです。

3どうか彼らが、きよく偉大な主の御名を、

恐れかしこみますように。

4公正なさばきを行うこと、

それこそが、この絶大な王の統治の基です。

イスラエル中に正しい判決が下ります。

5聖なる神である主をあがめ、

その足もとにひれ伏しなさい。

6預言者モーセとアロン、それにサムエルが

助けを呼び求めた時、主はお答えになりました。

7雲の柱の中から響いてくる声に、

彼らは従順に従いました。

8神である主よ。あなたは、人々の祈りに答えて

罪をお赦しになりましたが、

その誤った行為に対しては、

厳然として罰を下されました。

9私たちの神である主をあがめ、

エルサレムの聖なる山で礼拝しなさい。

神である主はきよいお方なのです。