መዝሙር 97 – NASV & KJV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 97:1-12

መዝሙር 97

የእግዚአብሔር ድል አድራጊነት

1እግዚአብሔር ነገሠ፤ ምድር ደስ ይበላት፤

በሩቅ ያሉ የባሕር ጠረፎች ሐሤት ያድርጉ።

2ደመናና ጥቅጥቅ ያለ ጭጋግ በዙሪያው አለ፤

ጽድቅና ፍትሕ የዙፋኑ መሠረት ናቸው።

3እሳት በፊቱ ይሄዳል፤

በዙሪያው ያሉትንም ጠላቶቹን ይፈጃል።

4መብረቁ ዓለምን አበራ፤

ምድርም አይታ ተንቀጠቀጠች።

5ተራሮች በእግዚአብሔር ፊት፣

በምድርም ሁሉ ጌታ ፊት እንደ ሰም ቀለጡ።

6ሰማያት ጽድቁን ያውጃሉ፤

ሕዝቦችም ሁሉ ክብሩን ያያሉ።

7ለተቀረጸ ምስል የሚሰግዱ፣

በጣዖታትም የሚመኩ ሁሉ ይፈሩ፤

እናንተ አማልክት ሁሉ፤ ለእርሱ ስገዱ።

8እግዚአብሔር ሆይ፤ ስለ ፍርድህ፣

ጽዮን ሰምታ ደስ አላት፤

የይሁዳም ሴት ልጆች ሐሤት አደረጉ።

9እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ በምድር ሁሉ ላይ ልዑል ነህና፤

ከአማልክትም ሁሉ በላይ እጅግ ከፍ ያልህ ነህ።

10እግዚአብሔርን የምትወድዱ ክፋትን ጥሉ፤

እርሱ የታማኞቹን ነፍስ ይጠብቃልና፤

ከዐመፀኞችም እጅ ይታደጋቸዋል።

11ብርሃን ለጻድቃን፣

ሐሤትም ልባቸው ለቀና ወጣ።

12እናንት ጻድቃን በእግዚአብሔር ደስ ይበላችሁ፤

ቅዱስ ስሙንም አመስግኑ።

King James Version

Psalms 97:1-12

1The LORD reigneth; let the earth rejoice; let the multitude of isles be glad thereof.97.1 multitude…: Heb. many, or, great isles

2Clouds and darkness are round about him: righteousness and judgment are the habitation of his throne.97.2 habitation: or, establishment

3A fire goeth before him, and burneth up his enemies round about.

4His lightnings enlightened the world: the earth saw, and trembled.

5The hills melted like wax at the presence of the LORD, at the presence of the Lord of the whole earth.

6The heavens declare his righteousness, and all the people see his glory.

7Confounded be all they that serve graven images, that boast themselves of idols: worship him, all ye gods.

8Zion heard, and was glad; and the daughters of Judah rejoiced because of thy judgments, O LORD.

9For thou, LORD, art high above all the earth: thou art exalted far above all gods.

10Ye that love the LORD, hate evil: he preserveth the souls of his saints; he delivereth them out of the hand of the wicked.

11Light is sown for the righteous, and gladness for the upright in heart.

12Rejoice in the LORD, ye righteous; and give thanks at the remembrance of his holiness.97.12 at…: or, to the memorial