መዝሙር 94 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 94:1-23

መዝሙር 94

የእግዚአብሔር ፍትሕ

1የበቀል አምላክ፣ አንተ እግዚአብሔር ሆይ፤

የበቀል አምላክ ሆይ፤ ደምቀህ ተገለጥ።

2አንተ የምድር ዳኛ ሆይ፤ ተነሥ፤

ለትዕቢተኞች የእጃቸውን ስጣቸው።

3ክፉዎች እስከ መቼ እግዚአብሔር ሆይ፤ ክፉዎች እስከ መቼ ይፈነጫሉ?

4የእብሪት ቃላት ያዥጐደጕዳሉ፤

ክፉ አድራጊዎች ሁሉ ጕራ ይነዛሉ።

5እግዚአብሔር ሆይ፤ ሕዝብህን አደቀቁ፤

ርስትህንም አስጨነቁ።

6መበለቲቱንና መጻተኛውን ገደሉ፤

የድኻ ዐደጉንም ነፍስ አጠፉ።

7እነርሱም “እግዚአብሔር አያይም፤

የያዕቆብም አምላክ አያስተውልም” አሉ።

8እናንት በሕዝቡ መካከል ያላችሁ ደነዞች፤ ልብ በሉ፤

እናንት ቂሎች፤ ጥበበኞች የምትሆኑት መቼ ነው?

9ጆሮን የተከለው እርሱ አይሰማምን? ዐይንንስ የሠራ እርሱ አያይምን?

10ሕዝቦችን በተግሣጽ ወደ መንገድ የሚመልስ፣

ዕውቀትንስ ለሰው ልጆች የሚያስተምር አይቀጣምን?

11እግዚአብሔር የሰው ሐሳብ መና፣

ከንቱም እንደ ሆነ ያውቃል።

12እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ የምትገሥጸው፣

ከሕግህም የምታስተምረው ሰው ምስጉን ነው።

13ለኀጢአተኞች ጕድጓድ እስኪማስላቸው ድረስ፣

እርሱን ከመከራ ታሳርፈዋለህ።

14እግዚአብሔር ሕዝቡን አይጥልምና፤

ርስቱንም አይተውም።

15ፍርድ ተመልሶ በጽድቅ አሠራር ላይ ይመሠረታል፤

ልባቸውም ቀና የሆነ ሁሉ ይከተሉታል።

16ክፉዎችን የሚቋቋምልኝ ማን ነው?

ከክፉ አድራጊዎችስ ጋር የሚሟገትልኝ ማን ነው?

17እግዚአብሔር ረዳቴ ባይሆን ኖሮ፣

ነፍሴ ወደ ዝምታው ዓለም ፈጥና በወረደች ነበር።

18እኔ፣ “እግሬ አዳለጠኝ” ባልሁ ጊዜ፣

እግዚአብሔር ሆይ፤ ምሕረትህ ደግፎ ያዘኝ።

19የውስጤ ጭንቀት በበዛ መጠን፣

ማጽናናትህ ነፍሴን ደስ አሰኛት።

20ዐመፃን ሕጋዊ የሚያደርግ፣

የጥፋት ዙፋን ከአንተ ጋር ሊያብር ይችላልን?

21በጻድቁ ላይ ተሰልፈው ይወጣሉ፤

በንጹሑም ላይ ሞት ይፈርዳሉ።

22ለእኔ ግን እግዚአብሔር ምሽግ፣

አምላኬም መጠጊያ ዐለት ሆኖኛል።

23በደላቸውን ወደ ራሳቸው ይመልሳል፤

በክፋታቸውም ያጠፋቸዋል፤

እግዚአብሔር አምላካችን ይደመስሳቸዋል።

Thai New Contemporary Bible

สดุดี 94:1-23

สดุดี 94

1ข้าแต่พระยาห์เวห์ พระเจ้าผู้ทรงแก้แค้น

ข้าแต่พระเจ้าผู้ทรงแก้แค้น ขอทรงสำแดงพระเกียรติสิริของพระองค์

2ข้าแต่องค์ตุลาการของโลก ขอทรงลุกขึ้นเถิด

ขอทรงตอบสนองคนหยิ่งผยองให้สาสม

3ข้าแต่องค์พระผู้เป็นเจ้า

นานเท่าใดที่คนชั่วจะลิงโลดในชัยชนะ?

4พวกเขาพล่ามวาจาโอหัง

คนทำชั่วทั้งปวงพร่ำคุยโม้โอ้อวด

5ข้าแต่องค์พระผู้เป็นเจ้า พวกเขาบดขยี้ประชากรของพระองค์

พวกเขาข่มเหงรังแกผู้เป็นกรรมสิทธิ์ของพระองค์

6พวกเขาสังหารหญิงม่ายและคนต่างด้าว

พวกเขาเข่นฆ่าลูกกำพร้าพ่อ

7พวกเขากล่าวว่า “องค์พระผู้เป็นเจ้าไม่ทรงรู้เห็น

พระเจ้าของยาโคบไม่ทรงใส่ใจ”

8เจ้าผู้ไม่รู้จักคิดในหมู่ประชากร จงใส่ใจ

คนโง่เอ๋ย เมื่อใดเจ้าจึงจะฉลาดขึ้น?

9พระองค์ผู้ทรงสร้างหูจะไม่ทรงได้ยินหรือ?

พระองค์ผู้ทรงสร้างตาจะไม่ทรงเห็นหรือ?

10พระองค์ผู้ทรงตีสั่งสอนประชาชาติจะไม่ทรงลงโทษหรือ?

พระองค์ผู้ทรงสอนมนุษย์จะขาดความรู้หรือ?

11องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงทราบความคิดของมนุษย์

ทรงรู้ว่าล้วนแต่เปล่าประโยชน์

12ข้าแต่องค์พระผู้เป็นเจ้า ความสุขมีแก่ผู้ที่พระองค์ทรงตีสั่งสอน

แก่ผู้ที่พระองค์ทรงสอนจากบทบัญญัติของพระองค์

13พระองค์ทรงให้พวกเขาได้รับความบรรเทาในยามเดือดร้อน

ตราบจนหลุมได้ขุดไว้สำหรับคนชั่ว

14เพราะองค์พระผู้เป็นเจ้าจะไม่ทรงปฏิเสธประชากรของพระองค์

พระองค์จะไม่ทรงละทิ้งผู้ที่เป็นกรรมสิทธิ์ของพระองค์

15การพิพากษาจะตั้งมั่นบนความชอบธรรมอีกครั้งหนึ่ง

และบรรดาผู้มีจิตใจเที่ยงธรรมจะดำเนินตามนั้น

16ใครจะลุกขึ้นต่อสู้กับคนชั่วเพื่อข้าพเจ้า?

ใครจะยืนหยัดต่อต้านคนทำชั่วเพื่อข้าพเจ้า?

17หากองค์พระผู้เป็นเจ้าไม่ได้ทรงช่วยข้าพเจ้าไว้

ในไม่ช้าข้าพเจ้าคงจะอยู่ในความเงียบแห่งความตาย

18เมื่อข้าพเจ้ากล่าวว่า “เท้าของข้าพระองค์กำลังลื่นไถล”

ข้าแต่องค์พระผู้เป็นเจ้าความรักมั่นคงของพระองค์ก็ค้ำชูข้าพระองค์ไว้

19เมื่อความวิตกกังวลสุมใจของข้าพระองค์

การปลอบประโลมของพระองค์ก็นำความชื่นชมยินดีมาสู่จิตวิญญาณของข้าพระองค์

20ผู้ครอบครองที่เสื่อมทรามจะอยู่ฝ่ายเดียวกับพระองค์ได้หรือ?

คือผู้เปล่งประกาศิตสร้างความทุกข์ยากแสนสาหัส

21พวกเขารวมตัวกันต่อสู้ผู้ชอบธรรม

และตัดสินประหารชีวิตผู้ที่ไม่มีความผิด

22แต่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงเป็นป้อมปราการของข้าพเจ้า

พระเจ้าองค์พระศิลาที่ข้าพเจ้าเข้าลี้ภัย

23พระองค์จะทรงให้พวกเขารับโทษสาสมกับบาปของพวกเขา

และทรงทำลายพวกเขาเพราะความชั่วร้ายของพวกเขาเอง

พระยาห์เวห์พระเจ้าของเราจะทรงทำลายล้างพวกเขา