መዝሙር 93 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 93:1-5

መዝሙር 93

የእግዚአብሔር ግርማ

1እግዚአብሔር ነገሠ፤ ግርማንም ተጐናጸፈ፤

እግዚአብሔር ግርማን ለበሰ፤

ብርታትንም ታጠቀ፤

ዓለም እንዳትናወጥ ጸንታለች፤

ማንም አይነቀንቃትም።

2ዙፋንህ ከጥንት ጀምሮ የጸና ነው፤

አንተም ከዘላለም እስከ ዘላለም አለህ።

3እግዚአብሔር ሆይ፤ ወንዞች ከፍ አደረጉ፤

ወንዞች ድምፃቸውን ከፍ አደረጉ፤

ወንዞች የሚያስገመግም ማዕበላቸውን ከፍ አደረጉ።

4ከብዙ ውሆች ድምፅ ይልቅ፣

ከባሕርም ሞገድ ይልቅ፣

ከፍ ብሎ ያለው እግዚአብሔር ኀያል ነው።

5ሥርዐትህ የጸና ነው፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ እስከ ዘላለሙ፣

ቤትህ በቅድስና ይዋባል።

Japanese Contemporary Bible

詩篇 93:1-5

93

1-2世界の王、主は、

威光と権能をまとっておられます。

ああ神よ。

永遠の昔から、あなたは世界を支配しておられます。

3大洋も鳴りとどろいて、

あなたを賛美しています。

4岸に打ち寄せ、白く砕け散る大波よりも

あなたは力強いお方です。

5そのおきては不変で、

その支配の原理は、きよさです。