መዝሙር 92 – NASV & NIV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 92:1-15

መዝሙር 92

ጻድቅ ሰው ሲደሰት

በሰንበት ቀን የሚዘመር መዝሙር፤ ማሕሌት።

1እግዚአብሔርን ማመስገን መልካም ነው፤

ልዑል ሆይ፤ ለስምህ መዘመር ጥሩ ነው፤

2ምሕረትህን በማለዳ፣

ታማኝነትህንም በሌሊት ማወጅ መልካም ነው፤

3ዐሥር አውታር ባለው በገና፣

በመሰንቆም ቅኝት ታጅቦ ማወጅ ጥሩ ነው።

4እግዚአብሔር ሆይ፤ በሥራህ ስለ ተደሰትሁ፣

ስለ እጅህ ሥራ በደስታ እዘምራለሁ።

5እግዚአብሔር ሆይ፤ ሥራህ እንዴት ታላቅ ነው!

ሐሳብህስ ምን ያህል ጥልቅ ነው!

6ደነዝ ሰው ይህን አያውቅም፤

ነኁላላም አያስተውለውም።

7ክፉዎች እንደ ሣር ቢበቅሉ፣

ክፉ አድራጊዎች ቢለመልሙ፣

ለዘላለሙ ይጠፋሉ፤

8እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ግን ለዘላለም ልዑል ነህ።

9ጠላቶችህ እግዚአብሔር ሆይ፤ ጠላቶችህ ይጠፋሉና፤

ክፉ አድራጊዎችም ሁሉ ይበተናሉ።

10የእኔን ቀንድ ግን እንደ አውራሪስ ቀንድ92፥10 ጥንካሬን የሚያመለክት ነው። ከፍ ከፍ አደረግኸው፤

በለጋ ዘይትም አረሰረስኸኝ።

11ዐይኖቼ የባላንጦቼን ውድቀት አዩ፤

ጆሮዎቼም የክፉ ጠላቶቼን ድቅቀት ሰሙ።

12ጻድቃን እንደ ዘንባባ ይንሰራፋሉ፤

እንደ ሊባኖስ ዝግባም ይንዠረገጋሉ።

13በእግዚአብሔር ቤት ተተክለዋል፤

በአምላካችንም አደባባይ ይንሰራፋሉ።

14ባረጁ ጊዜ እንኳ ያፈራሉ፤

እንደ ለመለሙና እንደ ጠነከሩም ይኖራሉ።

15እግዚአብሔር ትክክለኛ ነው፤

እርሱ ዐለቴ ነው፤ በእርሱ ዘንድ እንከን የለም” ይላሉ።

New International Version

Psalms 92:1-15

Psalm 92In Hebrew texts 92:1-15 is numbered 92:2-16.

A psalm. A song. For the Sabbath day.

1It is good to praise the Lord

and make music to your name, O Most High,

2proclaiming your love in the morning

and your faithfulness at night,

3to the music of the ten-stringed lyre

and the melody of the harp.

4For you make me glad by your deeds, Lord;

I sing for joy at what your hands have done.

5How great are your works, Lord,

how profound your thoughts!

6Senseless people do not know,

fools do not understand,

7that though the wicked spring up like grass

and all evildoers flourish,

they will be destroyed forever.

8But you, Lord, are forever exalted.

9For surely your enemies, Lord,

surely your enemies will perish;

all evildoers will be scattered.

10You have exalted my horn92:10 Horn here symbolizes strength. like that of a wild ox;

fine oils have been poured on me.

11My eyes have seen the defeat of my adversaries;

my ears have heard the rout of my wicked foes.

12The righteous will flourish like a palm tree,

they will grow like a cedar of Lebanon;

13planted in the house of the Lord,

they will flourish in the courts of our God.

14They will still bear fruit in old age,

they will stay fresh and green,

15proclaiming, “The Lord is upright;

he is my Rock, and there is no wickedness in him.”