መዝሙር 92 – NASV & KJV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 92:1-15

መዝሙር 92

ጻድቅ ሰው ሲደሰት

በሰንበት ቀን የሚዘመር መዝሙር፤ ማሕሌት።

1እግዚአብሔርን ማመስገን መልካም ነው፤

ልዑል ሆይ፤ ለስምህ መዘመር ጥሩ ነው፤

2ምሕረትህን በማለዳ፣

ታማኝነትህንም በሌሊት ማወጅ መልካም ነው፤

3ዐሥር አውታር ባለው በገና፣

በመሰንቆም ቅኝት ታጅቦ ማወጅ ጥሩ ነው።

4እግዚአብሔር ሆይ፤ በሥራህ ስለ ተደሰትሁ፣

ስለ እጅህ ሥራ በደስታ እዘምራለሁ።

5እግዚአብሔር ሆይ፤ ሥራህ እንዴት ታላቅ ነው!

ሐሳብህስ ምን ያህል ጥልቅ ነው!

6ደነዝ ሰው ይህን አያውቅም፤

ነኁላላም አያስተውለውም።

7ክፉዎች እንደ ሣር ቢበቅሉ፣

ክፉ አድራጊዎች ቢለመልሙ፣

ለዘላለሙ ይጠፋሉ፤

8እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ግን ለዘላለም ልዑል ነህ።

9ጠላቶችህ እግዚአብሔር ሆይ፤ ጠላቶችህ ይጠፋሉና፤

ክፉ አድራጊዎችም ሁሉ ይበተናሉ።

10የእኔን ቀንድ ግን እንደ አውራሪስ ቀንድ92፥10 ጥንካሬን የሚያመለክት ነው። ከፍ ከፍ አደረግኸው፤

በለጋ ዘይትም አረሰረስኸኝ።

11ዐይኖቼ የባላንጦቼን ውድቀት አዩ፤

ጆሮዎቼም የክፉ ጠላቶቼን ድቅቀት ሰሙ።

12ጻድቃን እንደ ዘንባባ ይንሰራፋሉ፤

እንደ ሊባኖስ ዝግባም ይንዠረገጋሉ።

13በእግዚአብሔር ቤት ተተክለዋል፤

በአምላካችንም አደባባይ ይንሰራፋሉ።

14ባረጁ ጊዜ እንኳ ያፈራሉ፤

እንደ ለመለሙና እንደ ጠነከሩም ይኖራሉ።

15እግዚአብሔር ትክክለኛ ነው፤

እርሱ ዐለቴ ነው፤ በእርሱ ዘንድ እንከን የለም” ይላሉ።

King James Version

Psalms 92:1-15

A Psalm or Song for the sabbath day.

1It is a good thing to give thanks unto the LORD, and to sing praises unto thy name, O most High:

2To shew forth thy lovingkindness in the morning, and thy faithfulness every night,92.2 every…: Heb. in the nights

3Upon an instrument of ten strings, and upon the psaltery; upon the harp with a solemn sound.92.3 the harp…: or, the solemn sound with the harp92.3 a solemn…: Heb. Higgaion

4For thou, LORD, hast made me glad through thy work: I will triumph in the works of thy hands.

5O LORD, how great are thy works! and thy thoughts are very deep.

6A brutish man knoweth not; neither doth a fool understand this.

7When the wicked spring as the grass, and when all the workers of iniquity do flourish; it is that they shall be destroyed for ever:

8But thou, LORD, art most high for evermore.

9For, lo, thine enemies, O LORD, for, lo, thine enemies shall perish; all the workers of iniquity shall be scattered.

10But my horn shalt thou exalt like the horn of an unicorn: I shall be anointed with fresh oil.

11Mine eye also shall see my desire on mine enemies, and mine ears shall hear my desire of the wicked that rise up against me.

12The righteous shall flourish like the palm tree: he shall grow like a cedar in Lebanon.

13Those that be planted in the house of the LORD shall flourish in the courts of our God.

14They shall still bring forth fruit in old age; they shall be fat and flourishing;92.14 flourishing: Heb. green

15To shew that the LORD is upright: he is my rock, and there is no unrighteousness in him.