መዝሙር 9 – NASV & NSP

New Amharic Standard Version

መዝሙር 9:1-20

መዝሙር 99 መዝ 9 እና 10 በመጀመሪያው የጥንት ቅጅ ላይ አንጓዎቹ ተከታታይ ፊደላት ባሉት የዕብራይስጥ ሆህያት የሚጀምሩ እንዲሁም ጅማሬው ወይም መጨረሻው ትርጕም ዐዘል የሆነ አንድ ወጥ ግጥም ነበር፤ በሰብዓ ሊቃናት ውስጥ ሁለቱም አንድ መዝሙር ናቸው።

በክፉ ላይ ፍርድ

ለመዘምራን አለቃ፤ በሙትላቤን ቅኝት፤ የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ በፍጹም ልቤ አመሰግንሃለሁ፤

ስለ ድንቅ ሥራዎችህም ሁሉ እናገራለሁ።

2በአንተ ደስ ይለኛል፤ ሐሤትም አደርጋለሁ፤

ልዑል ሆይ፤ ስምህን በመዝሙር እወድሳለሁ።

3ጠላቶቼ ወደ ኋላ በተመለሱ ጊዜ፣

ተሰነካክለው ከፊትህ ይጠፋሉ፤

4ፍርዴም ጕዳዬም በአንተ እጅ ናቸውና፤

ቅን ፍርድ እየሰጠህ በዙፋንህ ላይ ተቀምጠሃል።

5ሕዝቦችን ገሠጽህ፤ ክፉዎችንም አጠፋህ፤

ስማቸውንም እስከ ወዲያኛው ደመሰስህ።

6ጠላቶች ለዘላለም ጠፉ፤

ከተሞቻቸውንም ገለባበጥሃቸው፤

መታሰቢያቸውም ተደምስሷል።

7እግዚአብሔር ግን ለዘላለም በዙፋኑ ላይ ነው፤

መንበሩንም ለፍርድ አጽንቷል።

8ዓለምን በጽድቅ ይዳኛል፤

ሕዝቦችንም በፍትሕ ይገዛል።

9እግዚአብሔር ለተጨቈኑት ዐምባ ነው፤

በመከራም ጊዜ መጠጊያ ይሆናቸዋል።

10ስምህን የሚያውቁ ይታመኑብሃል፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ የሚሹህን አትተዋቸውምና።

11በጽዮን ለሚኖር ለእግዚአብሔር ዘምሩ፤

ሥራውንም በሕዝቦች መካከል በግልጽ አውሩ፤

12ደም ተበቃዩ ዐስቧቸዋልና፤

የጭቍኖችንም ጩኸት አልዘነጋም።

13እግዚአብሔር ሆይ፤ ጠላቶቼ የሚያደርሱብኝን መከራ ተመልከት፤

አይተህም ራራልኝ፤ ከሞት ደጅም አንሥተህ መልሰኝ፤

14ይህን ስታደርግልኝ፣ በጽዮን ሴት ልጅ ደጅ፣

ምስጋናህን ዐውጃለሁ፤

በማዳንህም ሐሤት አደርጋለሁ።

15አሕዛብ በቈፈሩት ጕድጓድ ገቡ፤

እግራቸውም ራሳቸው በስውር ባስቀመጡት ወጥመድ ተያዘ።

16እግዚአብሔር በትክክለኛ ፍርዱ የታወቀ ነው፤

ክፉዎችም በእጃቸው ሥራ ተጠመዱ። ሒጋዮን9፥16 ወይም በተመሥጦ ማሰብ ሴላ

17ክፉዎች ተመልሰው ወደ ሲኦል9፥17 ወይም መቃብር ይወርዳሉ፤

እግዚአብሔርን የሚዘነጉ ሕዝቦችም ሁሉ እንደዚሁ።

18ችግረኞች ግን መቼም ቢሆን አይረሱም፤

የድኾችም ተስፋ ለዘላለም መና ሆኖ አይቀርም።

19እግዚአብሔር ሆይ ተነሥ፤ ሰውም አያይል፤

አሕዛብም በፊትህ ይፈረድባቸው።

20እግዚአብሔር ሆይ፤ ድንጋጤ አምጣባቸው፤

ሕዝቦች ሰው ከመሆን እንደማያልፉ ይወቁ። ሴላ

New Serbian Translation

Псалми 9:1-20

Псалам 9

За хоровођу, по напеву „Смрт сина“. Псалам Давидов.

1Славићу Господа свим срцем својим,

причаћу о свим твојим чудесима.

2Веселићу се, теби ћу клицати,

твоме ћу имену певати, Свевишњи.

3Кад се моји непријатељи повуку у бегу,

нека се саплету и пропадну пред тобом.

4Јер ти си одбранио моје право и суд,

сео си на престо да судиш по правди.

5Укорио си народе, уништио опаке,

затро си им име у веке векова.

6Докрајчен је душманин,

у рушевинама је довека,

градове си му истребио,

спомен на њих избрисао.

7Али Господ столује до века,

престо је свој поставио да суди,

8и свету ће судити по правди,

једнако ће судити народима.

9Господ је заклон угњетеном,

заклон у време невоље.

10Нека се уздају у тебе они који твоје име знају,

јер ти, Господе, не остављаш оне што те траже.

11Певајте Господу, који столује на Сиону!

Причајте народима о делима његовим!

12Јер онај што се свети за проливену крв,

он памти, не заборавља вапај понизних.

13Смилуј ми се, о, Господе,

види како ме киње мрзитељи моји

– ти што ме извлачиш из врата смрти –

14да бих навештао сва славна дела твоја

на дверима ћерке сионске,

и тамо се радовао твојему спасењу.

15Народи јаму ископаше, ал’ у њу сами упадоше,

нога им се ухвати у мрежу коју сакрише.

16Господ је себе учинио знаним,

он поступа по праву,

а опаки се хвата у замку своје руке. Мисли. Села

17Нека се опаки врате у Свет мртвих,

сви народи који Бога заборављају,

18јер убоги неће увек бити заборављен,

нити пропасти нада понизних.

19Устани, Господе,

нека човек не надвлада,

нека се суди народима пред тобом.

20Утерај им страх у кости, Господе,

нека знају пуци да су само људи. Села