መዝሙር 9 – NASV & NIVUK

New Amharic Standard Version

መዝሙር 9:1-20

መዝሙር 99 መዝ 9 እና 10 በመጀመሪያው የጥንት ቅጅ ላይ አንጓዎቹ ተከታታይ ፊደላት ባሉት የዕብራይስጥ ሆህያት የሚጀምሩ እንዲሁም ጅማሬው ወይም መጨረሻው ትርጕም ዐዘል የሆነ አንድ ወጥ ግጥም ነበር፤ በሰብዓ ሊቃናት ውስጥ ሁለቱም አንድ መዝሙር ናቸው።

በክፉ ላይ ፍርድ

ለመዘምራን አለቃ፤ በሙትላቤን ቅኝት፤ የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ በፍጹም ልቤ አመሰግንሃለሁ፤

ስለ ድንቅ ሥራዎችህም ሁሉ እናገራለሁ።

2በአንተ ደስ ይለኛል፤ ሐሤትም አደርጋለሁ፤

ልዑል ሆይ፤ ስምህን በመዝሙር እወድሳለሁ።

3ጠላቶቼ ወደ ኋላ በተመለሱ ጊዜ፣

ተሰነካክለው ከፊትህ ይጠፋሉ፤

4ፍርዴም ጕዳዬም በአንተ እጅ ናቸውና፤

ቅን ፍርድ እየሰጠህ በዙፋንህ ላይ ተቀምጠሃል።

5ሕዝቦችን ገሠጽህ፤ ክፉዎችንም አጠፋህ፤

ስማቸውንም እስከ ወዲያኛው ደመሰስህ።

6ጠላቶች ለዘላለም ጠፉ፤

ከተሞቻቸውንም ገለባበጥሃቸው፤

መታሰቢያቸውም ተደምስሷል።

7እግዚአብሔር ግን ለዘላለም በዙፋኑ ላይ ነው፤

መንበሩንም ለፍርድ አጽንቷል።

8ዓለምን በጽድቅ ይዳኛል፤

ሕዝቦችንም በፍትሕ ይገዛል።

9እግዚአብሔር ለተጨቈኑት ዐምባ ነው፤

በመከራም ጊዜ መጠጊያ ይሆናቸዋል።

10ስምህን የሚያውቁ ይታመኑብሃል፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ የሚሹህን አትተዋቸውምና።

11በጽዮን ለሚኖር ለእግዚአብሔር ዘምሩ፤

ሥራውንም በሕዝቦች መካከል በግልጽ አውሩ፤

12ደም ተበቃዩ ዐስቧቸዋልና፤

የጭቍኖችንም ጩኸት አልዘነጋም።

13እግዚአብሔር ሆይ፤ ጠላቶቼ የሚያደርሱብኝን መከራ ተመልከት፤

አይተህም ራራልኝ፤ ከሞት ደጅም አንሥተህ መልሰኝ፤

14ይህን ስታደርግልኝ፣ በጽዮን ሴት ልጅ ደጅ፣

ምስጋናህን ዐውጃለሁ፤

በማዳንህም ሐሤት አደርጋለሁ።

15አሕዛብ በቈፈሩት ጕድጓድ ገቡ፤

እግራቸውም ራሳቸው በስውር ባስቀመጡት ወጥመድ ተያዘ።

16እግዚአብሔር በትክክለኛ ፍርዱ የታወቀ ነው፤

ክፉዎችም በእጃቸው ሥራ ተጠመዱ። ሒጋዮን9፥16 ወይም በተመሥጦ ማሰብ ሴላ

17ክፉዎች ተመልሰው ወደ ሲኦል9፥17 ወይም መቃብር ይወርዳሉ፤

እግዚአብሔርን የሚዘነጉ ሕዝቦችም ሁሉ እንደዚሁ።

18ችግረኞች ግን መቼም ቢሆን አይረሱም፤

የድኾችም ተስፋ ለዘላለም መና ሆኖ አይቀርም።

19እግዚአብሔር ሆይ ተነሥ፤ ሰውም አያይል፤

አሕዛብም በፊትህ ይፈረድባቸው።

20እግዚአብሔር ሆይ፤ ድንጋጤ አምጣባቸው፤

ሕዝቦች ሰው ከመሆን እንደማያልፉ ይወቁ። ሴላ

New International Version – UK

Psalms 9:1-20

Psalm 9Psalms 9 and 10 may originally have been a single acrostic poem in which alternating lines began with the successive letters of the Hebrew alphabet. In the Septuagint they constitute one psalm.In Hebrew texts 9:1-20 is numbered 9:2-21.

For the director of music. To the tune of ‘The Death of the Son’. A psalm of David.

1I will give thanks to you, Lord, with all my heart;

I will tell of all your wonderful deeds.

2I will be glad and rejoice in you;

I will sing the praises of your name, O Most High.

3My enemies turn back;

they stumble and perish before you.

4For you have upheld my right and my cause,

sitting enthroned as the righteous judge.

5You have rebuked the nations and destroyed the wicked;

you have blotted out their name for ever and ever.

6Endless ruin has overtaken my enemies,

you have uprooted their cities;

even the memory of them has perished.

7The Lord reigns for ever;

he has established his throne for judgment.

8He rules the world in righteousness

and judges the peoples with equity.

9The Lord is a refuge for the oppressed,

a stronghold in times of trouble.

10Those who know your name trust in you,

for you, Lord, have never forsaken those who seek you.

11Sing the praises of the Lord, enthroned in Zion;

proclaim among the nations what he has done.

12For he who avenges blood remembers;

he does not ignore the cries of the afflicted.

13Lord, see how my enemies persecute me!

Have mercy and lift me up from the gates of death,

14that I may declare your praises

in the gates of Daughter Zion,

and there rejoice in your salvation.

15The nations have fallen into the pit they have dug;

their feet are caught in the net they have hidden.

16The Lord is known by his acts of justice;

the wicked are ensnared by the work of their hands.9:16 The Hebrew has Higgaion and Selah (words of uncertain meaning) here; Selah occurs also at the end of verse 20.

17The wicked go down to the realm of the dead,

all the nations that forget God.

18But God will never forget the needy;

the hope of the afflicted will never perish.

19Arise, Lord, do not let mortals triumph;

let the nations be judged in your presence.

20Strike them with terror, Lord;

let the nations know they are only mortal.