መዝሙር 9 – NASV & KJV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 9:1-20

መዝሙር 99 መዝ 9 እና 10 በመጀመሪያው የጥንት ቅጅ ላይ አንጓዎቹ ተከታታይ ፊደላት ባሉት የዕብራይስጥ ሆህያት የሚጀምሩ እንዲሁም ጅማሬው ወይም መጨረሻው ትርጕም ዐዘል የሆነ አንድ ወጥ ግጥም ነበር፤ በሰብዓ ሊቃናት ውስጥ ሁለቱም አንድ መዝሙር ናቸው።

በክፉ ላይ ፍርድ

ለመዘምራን አለቃ፤ በሙትላቤን ቅኝት፤ የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ በፍጹም ልቤ አመሰግንሃለሁ፤

ስለ ድንቅ ሥራዎችህም ሁሉ እናገራለሁ።

2በአንተ ደስ ይለኛል፤ ሐሤትም አደርጋለሁ፤

ልዑል ሆይ፤ ስምህን በመዝሙር እወድሳለሁ።

3ጠላቶቼ ወደ ኋላ በተመለሱ ጊዜ፣

ተሰነካክለው ከፊትህ ይጠፋሉ፤

4ፍርዴም ጕዳዬም በአንተ እጅ ናቸውና፤

ቅን ፍርድ እየሰጠህ በዙፋንህ ላይ ተቀምጠሃል።

5ሕዝቦችን ገሠጽህ፤ ክፉዎችንም አጠፋህ፤

ስማቸውንም እስከ ወዲያኛው ደመሰስህ።

6ጠላቶች ለዘላለም ጠፉ፤

ከተሞቻቸውንም ገለባበጥሃቸው፤

መታሰቢያቸውም ተደምስሷል።

7እግዚአብሔር ግን ለዘላለም በዙፋኑ ላይ ነው፤

መንበሩንም ለፍርድ አጽንቷል።

8ዓለምን በጽድቅ ይዳኛል፤

ሕዝቦችንም በፍትሕ ይገዛል።

9እግዚአብሔር ለተጨቈኑት ዐምባ ነው፤

በመከራም ጊዜ መጠጊያ ይሆናቸዋል።

10ስምህን የሚያውቁ ይታመኑብሃል፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ የሚሹህን አትተዋቸውምና።

11በጽዮን ለሚኖር ለእግዚአብሔር ዘምሩ፤

ሥራውንም በሕዝቦች መካከል በግልጽ አውሩ፤

12ደም ተበቃዩ ዐስቧቸዋልና፤

የጭቍኖችንም ጩኸት አልዘነጋም።

13እግዚአብሔር ሆይ፤ ጠላቶቼ የሚያደርሱብኝን መከራ ተመልከት፤

አይተህም ራራልኝ፤ ከሞት ደጅም አንሥተህ መልሰኝ፤

14ይህን ስታደርግልኝ፣ በጽዮን ሴት ልጅ ደጅ፣

ምስጋናህን ዐውጃለሁ፤

በማዳንህም ሐሤት አደርጋለሁ።

15አሕዛብ በቈፈሩት ጕድጓድ ገቡ፤

እግራቸውም ራሳቸው በስውር ባስቀመጡት ወጥመድ ተያዘ።

16እግዚአብሔር በትክክለኛ ፍርዱ የታወቀ ነው፤

ክፉዎችም በእጃቸው ሥራ ተጠመዱ። ሒጋዮን9፥16 ወይም በተመሥጦ ማሰብ ሴላ

17ክፉዎች ተመልሰው ወደ ሲኦል9፥17 ወይም መቃብር ይወርዳሉ፤

እግዚአብሔርን የሚዘነጉ ሕዝቦችም ሁሉ እንደዚሁ።

18ችግረኞች ግን መቼም ቢሆን አይረሱም፤

የድኾችም ተስፋ ለዘላለም መና ሆኖ አይቀርም።

19እግዚአብሔር ሆይ ተነሥ፤ ሰውም አያይል፤

አሕዛብም በፊትህ ይፈረድባቸው።

20እግዚአብሔር ሆይ፤ ድንጋጤ አምጣባቸው፤

ሕዝቦች ሰው ከመሆን እንደማያልፉ ይወቁ። ሴላ

King James Version

Psalms 9:1-20

To the chief Musician upon Muthlabben, A Psalm of David.

1I will praise thee, O LORD, with my whole heart; I will shew forth all thy marvellous works.

2I will be glad and rejoice in thee: I will sing praise to thy name, O thou most High.

3When mine enemies are turned back, they shall fall and perish at thy presence.

4For thou hast maintained my right and my cause; thou satest in the throne judging right.9.4 maintained…: Heb. made my judgment9.4 judging right: Heb. judging in righteousness

5Thou hast rebuked the heathen, thou hast destroyed the wicked, thou hast put out their name for ever and ever.

6O thou enemy, destructions are come to a perpetual end: and thou hast destroyed cities; their memorial is perished with them.9.6 O thou…: or, The destructions of the enemy are come to a perpetual end: and their cities hast thou destroyed, etc

7But the LORD shall endure for ever: he hath prepared his throne for judgment.

8And he shall judge the world in righteousness, he shall minister judgment to the people in uprightness.

9The LORD also will be a refuge for the oppressed, a refuge in times of trouble.9.9 a refuge: Heb. an high place

10And they that know thy name will put their trust in thee: for thou, LORD, hast not forsaken them that seek thee.

11Sing praises to the LORD, which dwelleth in Zion: declare among the people his doings.

12When he maketh inquisition for blood, he remembereth them: he forgetteth not the cry of the humble.9.12 humble: or, afflicted

13Have mercy upon me, O LORD; consider my trouble which I suffer of them that hate me, thou that liftest me up from the gates of death:

14That I may shew forth all thy praise in the gates of the daughter of Zion: I will rejoice in thy salvation.

15The heathen are sunk down in the pit that they made: in the net which they hid is their own foot taken.

16The LORD is known by the judgment which he executeth: the wicked is snared in the work of his own hands. Higgaion. Selah.9.16 Higgaion: that is, Meditation

17The wicked shall be turned into hell, and all the nations that forget God.

18For the needy shall not alway be forgotten: the expectation of the poor shall not perish for ever.

19Arise, O LORD; let not man prevail: let the heathen be judged in thy sight.

20Put them in fear, O LORD: that the nations may know themselves to be but men. Selah.