መዝሙር 87 – NASV & NUB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 87:1-7

መዝሙር 87

ጽዮን የሕዝቦች እናት

የቆሬ ልጆች መዝሙር፤ ማሕሌት።

1መሠረቱን በተቀደሱ ተራሮች አቆመ፤

2እግዚአብሔር ከያዕቆብ ማደሪያዎች ሁሉ ይልቅ፣

የጽዮንን ደጆች ይወድዳል።

3የእግዚአብሔር ከተማ ሆይ፤

ስለ አንቺ ክቡር የሆነ ነገር እንዲህ ተብሎ ይነገራል፤ ሴላ

4“ከሚያውቁኝ መካከል፣

ረዓብንና87፥4 የግብፅ ቅኔያዊ ስያሜ ነው። ባቢሎንን እጠቅሳለሁ፤

እነሆ፤ ፍልስጥኤምና ጢሮስ ከኢትዮጵያ ጋር፣87፥4 ወይም ረዓብ ባቢሎን፣ ፍልስጥኤምና ኢትዮጵያ

‘ይህ ሰው በዚያ ነው የተወለደው’ ይላሉ።”

5በርግጥም ስለ ጽዮን፣

“ይህም ያም ሰው በእርሷ ውስጥ ተወለዱ፤

ልዑልም ራሱ ያጸናታል” ይባላል።

6እግዚአብሔር ሕዝቡን ሲመዘግብ፣

“ይህ ሰው የተወለደው በዚያ ነው” ብሎ ይጽፋል። ሴላ

7የሚያዜሙም መሣሪያ የሚጫወቱም፣

“ምንጩ ሁሉ በአንቺ ውስጥ ይገኛል” ይላሉ።

Swedish Contemporary Bible

Psaltaren 87:1-7

Psalm 87

Sion

1Av Korachs ättlingar. En psalm, en sång.

Dess grund är lagd på de heliga bergen.

2Herren älskar Sions portar

mer än någon annan av Jakobs boningar.

3Härliga ting talas om dig,

Guds stad. Séla

4”Bland dem som känner mig

ska jag räkna Rahav87:4 Representerar Egypten. och Babylonien

och också Filisteen, Tyros och Kush.

Dessa är födda här.”

5Man ska säga om Sion: ”Var och en är född här.”

Den Högste har grundat denna stad.

6Herren skriver i listan över folken:

”Dessa är födda där.” Séla

7Man ska sjunga och dansa:

”Alla mina källor finns hos dig.”