መዝሙር 82 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 82:1-8

መዝሙር 82

ሙሱናን ዳኞች

የአሳፍ መዝሙር።

1እግዚአብሔር በአማልክት ጉባኤ መካከል ተሰየመ፤

በአማልክትም ላይ ይፈርዳል፤ እንዲህም ይላል፤

2“ፍትሕን የምታጓድሉት እስከ መቼ ነው?

ለክፉዎች የምታደሉትስ እስከ መቼ ነው? ሴላ

3ለዐቅመ ቢሶችና ለድኻ ዐደጎች ፍረዱላቸው፤

የችግረኛውንና የምስኪኑን መብት አስከብሩ።

4ወገን የሌለውንና ችግረኛውን ታደጉ፤

ከግፈኛውም እጅ አስጥሏቸው።

5“ዕውቀትም ማስተዋልም የላቸውም፤

በጨለማ ውስጥ ወዲያ ወዲህ ይመላለሳሉ፤

የምድርም መሠረቶች ሁሉ ተናወጡ።

6“እኔም፤ ‘እናንተ አማልክት ናችሁ፤

ሁላችሁም የልዑል ልጆች ናችሁ’ አልሁ።

7ነገር ግን እንደ ማንኛውም ሰው ትሞታላችሁ፤

እንደ ማንኛውም ገዥ ትወድቃላችሁ።”

8አምላክ ሆይ፤ ተነሥ፤ በምድር ላይ ፍረድ፣

ሕዝቦች ሁሉ ርስትህ ናቸውና።

Thai New Contemporary Bible

สดุดี 82:1-8

สดุดี 82

(บทสดุดีของอาสาฟ)

1พระเจ้าทรงเป็นประธานในการประชุมใหญ่

พระองค์ทรงประกาศคำตัดสินท่ามกลาง “เทพเจ้าทั้งหลาย” ว่า

2“พวกเจ้าจะตัดสินอย่างอยุติธรรม

และลำเอียงเข้าข้างคนชั่วไปนานสักเท่าใด?

เสลาห์

3จงให้ความยุติธรรมแก่ผู้อ่อนแอและลูกกำพร้าพ่อ

จงผดุงสิทธิของผู้ตกทุกข์ได้ยากและผู้ถูกกดขี่ข่มเหง

4จงช่วยกู้ผู้อ่อนแอและขัดสน

ปลดปล่อยเขาจากเงื้อมมือของคนชั่วร้าย

5“พวกเขาไม่รู้ไม่เข้าใจอะไรเลย

พวกเขาต่างเดินวนเวียนอยู่ในความมืด

รากฐานทั้งมวลของโลกจึงสั่นคลอน

6“เรากล่าวว่า ‘พวกเจ้าเป็น “เทพเจ้า”

และพวกเจ้าล้วนเป็นบุตรขององค์ผู้สูงสุด’

7แต่เจ้าจะตายเยี่ยงมนุษย์ปุถุชน

เจ้าจะล้มลงเหมือนเจ้านายคนอื่นๆ ทุกคน”

8ข้าแต่พระเจ้า ขอทรงลุกขึ้นพิพากษาโลก

เพราะมวลประชาชาติเป็นกรรมสิทธิ์ของพระองค์