መዝሙር 82 – NASV & NSP

New Amharic Standard Version

መዝሙር 82:1-8

መዝሙር 82

ሙሱናን ዳኞች

የአሳፍ መዝሙር።

1እግዚአብሔር በአማልክት ጉባኤ መካከል ተሰየመ፤

በአማልክትም ላይ ይፈርዳል፤ እንዲህም ይላል፤

2“ፍትሕን የምታጓድሉት እስከ መቼ ነው?

ለክፉዎች የምታደሉትስ እስከ መቼ ነው? ሴላ

3ለዐቅመ ቢሶችና ለድኻ ዐደጎች ፍረዱላቸው፤

የችግረኛውንና የምስኪኑን መብት አስከብሩ።

4ወገን የሌለውንና ችግረኛውን ታደጉ፤

ከግፈኛውም እጅ አስጥሏቸው።

5“ዕውቀትም ማስተዋልም የላቸውም፤

በጨለማ ውስጥ ወዲያ ወዲህ ይመላለሳሉ፤

የምድርም መሠረቶች ሁሉ ተናወጡ።

6“እኔም፤ ‘እናንተ አማልክት ናችሁ፤

ሁላችሁም የልዑል ልጆች ናችሁ’ አልሁ።

7ነገር ግን እንደ ማንኛውም ሰው ትሞታላችሁ፤

እንደ ማንኛውም ገዥ ትወድቃላችሁ።”

8አምላክ ሆይ፤ ተነሥ፤ በምድር ላይ ፍረድ፣

ሕዝቦች ሁሉ ርስትህ ናቸውና።

New Serbian Translation

Псалми 82:1-8

Псалам 82

Псалам Асафов.

1Бог је стао у Божијем збору,

па сад суди међу боговима:

2„Докле ћете судити нечасно

и држати страну злотворима? Села

3Заступајте право убогога и сиротога,

оправдајте сиромаха и невољника.

4Спасавајте слабог и тлаченог,

избавите их из руке зликоваца.

5Али нису знали, нису разумели;

у тами су посртали

и темеље земљи задрмали.

6Ја рекох: ’Богови сте,

сви сте деца Свевишњега!’

7Ипак ћете помрети ко људи,

пропашћете ко и главар сваки.“

8Устани, Боже, и суди земљи,

јер сви су народи наследство твоје!