መዝሙር 82 – NASV & KJV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 82:1-8

መዝሙር 82

ሙሱናን ዳኞች

የአሳፍ መዝሙር።

1እግዚአብሔር በአማልክት ጉባኤ መካከል ተሰየመ፤

በአማልክትም ላይ ይፈርዳል፤ እንዲህም ይላል፤

2“ፍትሕን የምታጓድሉት እስከ መቼ ነው?

ለክፉዎች የምታደሉትስ እስከ መቼ ነው? ሴላ

3ለዐቅመ ቢሶችና ለድኻ ዐደጎች ፍረዱላቸው፤

የችግረኛውንና የምስኪኑን መብት አስከብሩ።

4ወገን የሌለውንና ችግረኛውን ታደጉ፤

ከግፈኛውም እጅ አስጥሏቸው።

5“ዕውቀትም ማስተዋልም የላቸውም፤

በጨለማ ውስጥ ወዲያ ወዲህ ይመላለሳሉ፤

የምድርም መሠረቶች ሁሉ ተናወጡ።

6“እኔም፤ ‘እናንተ አማልክት ናችሁ፤

ሁላችሁም የልዑል ልጆች ናችሁ’ አልሁ።

7ነገር ግን እንደ ማንኛውም ሰው ትሞታላችሁ፤

እንደ ማንኛውም ገዥ ትወድቃላችሁ።”

8አምላክ ሆይ፤ ተነሥ፤ በምድር ላይ ፍረድ፣

ሕዝቦች ሁሉ ርስትህ ናቸውና።

King James Version

Psalms 82:1-8

A Psalm of Asaph.

1God standeth in the congregation of the mighty; he judgeth among the gods.82.1 of Asaph: or, for Asaph

2How long will ye judge unjustly, and accept the persons of the wicked? Selah.

3Defend the poor and fatherless: do justice to the afflicted and needy.82.3 Defend: Heb. Judge

4Deliver the poor and needy: rid them out of the hand of the wicked.

5They know not, neither will they understand; they walk on in darkness: all the foundations of the earth are out of course.82.5 out…: Heb. moved

6I have said, Ye are gods; and all of you are children of the most High.

7But ye shall die like men, and fall like one of the princes.

8Arise, O God, judge the earth: for thou shalt inherit all nations.