መዝሙር 82 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 82:1-8

መዝሙር 82

ሙሱናን ዳኞች

የአሳፍ መዝሙር።

1እግዚአብሔር በአማልክት ጉባኤ መካከል ተሰየመ፤

በአማልክትም ላይ ይፈርዳል፤ እንዲህም ይላል፤

2“ፍትሕን የምታጓድሉት እስከ መቼ ነው?

ለክፉዎች የምታደሉትስ እስከ መቼ ነው? ሴላ

3ለዐቅመ ቢሶችና ለድኻ ዐደጎች ፍረዱላቸው፤

የችግረኛውንና የምስኪኑን መብት አስከብሩ።

4ወገን የሌለውንና ችግረኛውን ታደጉ፤

ከግፈኛውም እጅ አስጥሏቸው።

5“ዕውቀትም ማስተዋልም የላቸውም፤

በጨለማ ውስጥ ወዲያ ወዲህ ይመላለሳሉ፤

የምድርም መሠረቶች ሁሉ ተናወጡ።

6“እኔም፤ ‘እናንተ አማልክት ናችሁ፤

ሁላችሁም የልዑል ልጆች ናችሁ’ አልሁ።

7ነገር ግን እንደ ማንኛውም ሰው ትሞታላችሁ፤

እንደ ማንኛውም ገዥ ትወድቃላችሁ።”

8አምላክ ሆይ፤ ተነሥ፤ በምድር ላይ ፍረድ፣

ሕዝቦች ሁሉ ርስትህ ናቸውና።

Japanese Contemporary Bible

詩篇 82:1-8

82

1神は、天の法廷を開いて、

裁判官たちに判決をお授けになります。

2いつまでおまえたち裁判官は、

真実の証言に耳をふさぐのか。

いつまで悪党どもに便宜をはかっているのか。

3貧しい者、悩む者、身寄りのない者、

日々の暮らしに事欠く者を公平にさばけ。

4悪い者たちから、

貧乏で苦しんでいる人々を救い出せ。

5ところが、おまえたちは、何も知らない愚か者なのだ。

おまえたちが暗闇に閉じ込められているため、

社会の土台は根本から揺らいでいる。

6わたしはおまえたちを「神々」とか

「いと高き神の子たち」と呼んだが、

7いずれは死んでしまう、ただの人間なのだ。

王族も同じだ。人間はみな死ぬ運命にある。

8ああ神よ、立ち上がって、この世をさばいてください。

地にあるものはみな神のもので、

諸国はあなたの手の中にあります。