መዝሙር 82 – NASV & HTB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 82:1-8

መዝሙር 82

ሙሱናን ዳኞች

የአሳፍ መዝሙር።

1እግዚአብሔር በአማልክት ጉባኤ መካከል ተሰየመ፤

በአማልክትም ላይ ይፈርዳል፤ እንዲህም ይላል፤

2“ፍትሕን የምታጓድሉት እስከ መቼ ነው?

ለክፉዎች የምታደሉትስ እስከ መቼ ነው? ሴላ

3ለዐቅመ ቢሶችና ለድኻ ዐደጎች ፍረዱላቸው፤

የችግረኛውንና የምስኪኑን መብት አስከብሩ።

4ወገን የሌለውንና ችግረኛውን ታደጉ፤

ከግፈኛውም እጅ አስጥሏቸው።

5“ዕውቀትም ማስተዋልም የላቸውም፤

በጨለማ ውስጥ ወዲያ ወዲህ ይመላለሳሉ፤

የምድርም መሠረቶች ሁሉ ተናወጡ።

6“እኔም፤ ‘እናንተ አማልክት ናችሁ፤

ሁላችሁም የልዑል ልጆች ናችሁ’ አልሁ።

7ነገር ግን እንደ ማንኛውም ሰው ትሞታላችሁ፤

እንደ ማንኛውም ገዥ ትወድቃላችሁ።”

8አምላክ ሆይ፤ ተነሥ፤ በምድር ላይ ፍረድ፣

ሕዝቦች ሁሉ ርስትህ ናቸውና።

Het Boek

Psalmen 82:1-8

1Een psalm van Asaf.

God staat te midden van de bijeenkomst van de goden,

Hij treedt in hun midden als rechter op.

2Het lijkt wel of U de ongelovigen recht verschaft

en ons niet. Hoelang moet dat nog duren?

3Spreek uw oordeel uit over armen en wezen,

laat het recht zegevieren voor de armzaligen

en hen die niets hebben.

4Bevrijd de man die wordt vernederd en de arme,

red hen uit de handen van de misdadigers.

5Zij zijn dom en kunnen niets vatten,

zij lopen in het donker en de aarde wankelt onder uw voeten.

6Toch heb Ik gezegd:

‘U bent goden, kinderen van de Allerhoogste, allemaal.’

7Net als andere mensen zullen zij sterven

en vallen als overwonnen koningen.

8Kom, God, spreek recht over de aarde.

Alle volken zijn immers van U?