መዝሙር 79 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

መዝሙር 79:1-13

መዝሙር 79

ብሔራዊ ሰቈቃ

የአሳፍ መዝሙር።

1አምላክ ሆይ፤ ሕዝቦች ርስትህን ወረሩ፤

የተቀደሰውን ቤተ መቅደስህን አረከሱ፤

ኢየሩሳሌምንም አፈራርሰው ጣሏት።

2የባሪያዎችህን ሬሳ ለሰማይ ወፎች፣

የቅዱሳንህንም ሥጋ ለምድር አራዊት፣

ምግብ አድርገው ሰጡ።

3ደማቸውንም በኢየሩሳሌም ዙሪያ፣

እንደ ውሃ አፈሰሱ፤

የሚቀብራቸውም አልተገኘም።

4እኛም ለጎረቤቶቻችን መዘባበቻ፣

በዙሪያችንም ላሉት መሣቂያ መሣለቂያ ሆንን።

5እግዚአብሔር ሆይ፤ ይህ እስከ መቼ ነው?

የምትቈጣውስ ለዘላለም ነውን?

ቅናትህስ እንደ እሳት ሲነድድ ይኖራልን?

6በማያውቁህ ሕዝቦች ላይ፣

ስምህን በማይጠሩ፣

መንግሥታት ላይ፣

መዓትህን አፍስስ፤

7ያዕቆብን በልተውታልና፤

መኖሪያ ቦታውንም ባድማ አድርገዋል።

8የአባቶቻችንን ኀጢአት በእኛ ላይ አትቍጠርብን፤

ምሕረትህ ፈጥና ወደ እኛ ትምጣ፤

በጭንቅ ላይ እንገኛለንና።

9አዳኛችን የሆንህ አምላክ ሆይ፤

ስለ ስምህ ክብር ብለህ ርዳን፤

ስለ ስምህ ስትል፣

ታደገን፤ ኀጢአታችንንም ይቅር በል።

10ሕዝቦች፣ “አምላካቸው የት አለ?”

ለምን ይበሉ?

የፈሰሰውን የአገልጋዮችህን ደም በቀል፣

ዐይናችን እያየ ሕዝቦች ይወቁት።

11የእስረኞች ሰቈቃ በፊትህ ይድረስ፤

በክንድህም ብርታት፣

ሞት የተፈረደባቸውን አድን።

12ጌታ ሆይ፤ ጎረቤቶቻችን በአንተ ላይ የተዘባበቱትን መዘባበት፣

ሰባት ዕጥፍ አድርገህ አስታቅፋቸው።

13እኛ ሕዝብህ፣ የማሰማሪያህ በጎችህ፣

ለዘላለም ምስጋና እናቀርብልሃለን፤

ከትውልድ እስከ ትውልድም፣

ውለታህን እንናገራለን።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

詩篇 79:1-13

第 79 篇

祈求上帝拯救

亞薩的詩。

1上帝啊,

外族人侵佔你的產業,

玷污你的聖殿,

使耶路撒冷淪為廢墟。

2他們把你僕人的屍體餵飛鳥,

把你忠心子民的屍體給野獸吃,

3使耶路撒冷周圍血流成河,

屍體無人埋葬。

4我們成了列國羞辱的對象,

周圍的人都嗤笑、譏諷我們。

5耶和華啊,你向我們發怒,

要到何時呢?

難道要到永遠嗎?

你的怒火要燒到何時呢?

6求你把烈怒撒向那些不承認你的列邦,

撒向那些不求告你的列國。

7因為他們吞噬了雅各

摧毀了他的家園。

8求你不要向我們追討我們祖先的罪,

願你快快地憐憫我們,

因為我們已經落入絕望中。

9拯救我們的上帝啊,

求你為了自己榮耀的名而幫助我們,

為你名的緣故拯救我們,

赦免我們的罪。

10為何讓列邦說:

「他們的上帝在哪裡?」

求你讓我們親眼看見,

也讓列邦都知道,

你為自己被害的子民伸冤。

11求你垂聽被囚之人的哀歎,

求你用大能的臂膀留住死囚的性命。

12主啊,我們的鄰邦羞辱你,

求你以七倍的羞辱來報應他們。

13這樣,你的子民,你草場上的羊必永遠稱謝你,世代稱頌你。