መዝሙር 79 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 79:1-13

መዝሙር 79

ብሔራዊ ሰቈቃ

የአሳፍ መዝሙር።

1አምላክ ሆይ፤ ሕዝቦች ርስትህን ወረሩ፤

የተቀደሰውን ቤተ መቅደስህን አረከሱ፤

ኢየሩሳሌምንም አፈራርሰው ጣሏት።

2የባሪያዎችህን ሬሳ ለሰማይ ወፎች፣

የቅዱሳንህንም ሥጋ ለምድር አራዊት፣

ምግብ አድርገው ሰጡ።

3ደማቸውንም በኢየሩሳሌም ዙሪያ፣

እንደ ውሃ አፈሰሱ፤

የሚቀብራቸውም አልተገኘም።

4እኛም ለጎረቤቶቻችን መዘባበቻ፣

በዙሪያችንም ላሉት መሣቂያ መሣለቂያ ሆንን።

5እግዚአብሔር ሆይ፤ ይህ እስከ መቼ ነው?

የምትቈጣውስ ለዘላለም ነውን?

ቅናትህስ እንደ እሳት ሲነድድ ይኖራልን?

6በማያውቁህ ሕዝቦች ላይ፣

ስምህን በማይጠሩ፣

መንግሥታት ላይ፣

መዓትህን አፍስስ፤

7ያዕቆብን በልተውታልና፤

መኖሪያ ቦታውንም ባድማ አድርገዋል።

8የአባቶቻችንን ኀጢአት በእኛ ላይ አትቍጠርብን፤

ምሕረትህ ፈጥና ወደ እኛ ትምጣ፤

በጭንቅ ላይ እንገኛለንና።

9አዳኛችን የሆንህ አምላክ ሆይ፤

ስለ ስምህ ክብር ብለህ ርዳን፤

ስለ ስምህ ስትል፣

ታደገን፤ ኀጢአታችንንም ይቅር በል።

10ሕዝቦች፣ “አምላካቸው የት አለ?”

ለምን ይበሉ?

የፈሰሰውን የአገልጋዮችህን ደም በቀል፣

ዐይናችን እያየ ሕዝቦች ይወቁት።

11የእስረኞች ሰቈቃ በፊትህ ይድረስ፤

በክንድህም ብርታት፣

ሞት የተፈረደባቸውን አድን።

12ጌታ ሆይ፤ ጎረቤቶቻችን በአንተ ላይ የተዘባበቱትን መዘባበት፣

ሰባት ዕጥፍ አድርገህ አስታቅፋቸው።

13እኛ ሕዝብህ፣ የማሰማሪያህ በጎችህ፣

ለዘላለም ምስጋና እናቀርብልሃለን፤

ከትውልድ እስከ ትውልድም፣

ውለታህን እንናገራለን።

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

诗篇 79:1-13

第 79 篇

祈求上帝拯救

亚萨的诗。

1上帝啊,

外族人侵占你的产业,

玷污你的圣殿,

使耶路撒冷沦为废墟。

2他们把你仆人的尸体喂飞鸟,

把你忠心子民的尸体给野兽吃,

3使耶路撒冷周围血流成河,

尸体无人埋葬。

4我们成了列国羞辱的对象,

周围的人都嗤笑、讥讽我们。

5耶和华啊,你向我们发怒,

要到何时呢?

难道要到永远吗?

你的怒火要烧到何时呢?

6求你把烈怒撒向那些不承认你的列邦,

撒向那些不求告你的列国。

7因为他们吞噬了雅各

摧毁了他的家园。

8求你不要向我们追讨我们祖先的罪,

愿你快快地怜悯我们,

因为我们已经落入绝望中。

9拯救我们的上帝啊,

求你为了自己荣耀的名而帮助我们,

为你名的缘故拯救我们,

赦免我们的罪。

10为何让列邦说:

“他们的上帝在哪里?”

求你让我们亲眼看见,

也让列邦都知道,

你为自己被害的子民申冤。

11求你垂听被囚之人的哀叹,

求你用大能的臂膀留住死囚的性命。

12主啊,我们的邻邦羞辱你,

求你以七倍的羞辱来报应他们。

13这样,你的子民,你草场上的羊必永远称谢你,世代称颂你。