መዝሙር 78 – NASV & NIVUK

New Amharic Standard Version

መዝሙር 78:1-72

መዝሙር 78

በእስራኤል የተገኘ ታሪክ

የአሳፍ ትምህርት።

1ሕዝቤ ሆይ፤ ትምህርቴን ስማ፤

ጆሮህንም ወደ አንደበቴ ቃል አዘንብል።

2አፌን በምሳሌ እከፍታለሁ፤

ከጥንት በነበረ እንቈቅልሽ እናገራለሁ፤

3ይህም የሰማነውና ያወቅነው፣

አባቶቻችንም የነገሩን ነው።

4እኛም ከልጆቻቸው አንደብቀውም፤

የእግዚአብሔርን ምስጋና፣

ኀይሉንና ያደረገውን ድንቅ ሥራ፣

ለሚቀጥለው ትውልድ እንናገራለን።

5ለያዕቆብ ሥርዐትን መሠረተ፤

በእስራኤልም ሕግን ደነገገ፤

ልጆቻቸውንም እንዲያስተምሩ፣

አባቶቻችንን አዘዘ።

6ይህም የሚቀጥለው ትውልድ እንዲያውቅ፣

እነርሱም በተራቸው ለልጆቻቸው፣

ገና ለሚወለዱትም እንዲነግሩ ነው።

7እነርሱም በእግዚአብሔር ይታመናሉ፤

የእርሱንም ሥራ አይረሱም፤

ትእዛዞቹንም ይጠብቃሉ።

8ነገር ግን እንደ አባቶቻቸው፣

እልኸኞችና ዐመፀኞች፣

ልቡን ያላቀና፣

መንፈሱም በእግዚአብሔር የማይታመን ትውልድ አይሆኑም።

9የኤፍሬም ልጆች የታጠቁ ቀስተኞች ቢሆኑም፣

በጦርነት ቀን ወደ ኋላ ተመለሱ።

10የእግዚአብሔርን ኪዳን አልጠበቁም፤ በሕጉም መሠረት ለመሄድ እንቢ አሉ።

11እርሱ የሠራውን ሥራ፣

ያሳያቸውንም ድንቅ ነገር ረሱ።

12አባቶቻቸው በዐይናቸው እያዩ፣

በግብፅ አገር፣ በጣኔዎስ ምድር ታምራት አደረገ።

13ባሕሩን ከፍሎ አሻገራቸው፤

ውሃውንም እንደ ክምር አቆመ።

14ቀን በደመና መራቸው፤

ሌሊቱንም ሁሉ በእሳት ብርሃን።

15ዐለቱን በምድረ በዳ ሰነጠቀ፤

እንደ ባሕር የበዛ ውሃ አጠጣቸው፤

16ምንጭ ከቋጥኝ አፈለቀ፤

ውሃን እንደ ወንዝ አወረደ።

17እነርሱ ግን በምድረ በዳ በልዑል ላይ በማመፅ፣

በእርሱ ላይ ኀጢአት መሥራታቸውን ቀጠሉ።

18እጅግ የተመኙትን ምግብ በመጠየቅ፣

እግዚአብሔርን በልባቸው ተፈታተኑት።

19እንዲህም ብለው በእግዚአብሔር ላይ ተናገሩ፤

“እግዚአብሔር በምድረ በዳ ማእድ ማሰናዳት ይችላልን?

20ዐለቱን ሲመታ፣ ውሃ ተንዶለዶለ፤

ጅረቶችም ጐረፉ፤

ታዲያ፣ እንጀራንም መስጠት ይችላል?

ሥጋንስ ለሕዝቡ ሊያቀርብ ይችላል?”

21እግዚአብሔር ይህን ሲሰማ፣ እጅግ ተቈጣ፤

በያዕቆብም ላይ እሳት ነደደ፤

ቍጣውም በእስራኤል ላይ ተነሣ፤

22በእግዚአብሔር አላመኑምና፤

በእርሱም ማዳን አልታመኑም።

23እርሱ ግን ከላይ ደመናትን አዘዘ፤

የሰማይንም ደጆች ከፈተ፤

24ይበሉም ዘንድ መና አዘነበላቸው፤

የሰማይንም መብል ሰጣቸው።

25ሰዎች የመላእክትን እንጀራ በሉ፤

ጠግበው እስከሚተርፍ ድረስ ምግብ ላከላቸው።

26የምሥራቁን ነፋስ ከሰማይ አስነሣ፤

የደቡብንም ነፋስ በኀይሉ አመጣ።

27ሥጋን እንደ ዐፈር፣

የሚበሩትን ወፎች እንደ ባሕር አሸዋ አዘነበላቸው፤

28በሰፈራቸውም ውስጥ፣

በድንኳናቸው ዙሪያ አወረደ።

29እነርሱም እስኪጠግቡ ድረስ በሉ፤

እጅግ የጐመጁትን ሰጥቷቸዋልና።

30ነገር ግን ገና ምኞታቸውን ሳያረኩ፣

ምግቡ ገና በአፋቸው ውስጥ እያለ፣

31የእግዚአብሔር ቍጣ በላያቸው ላይ መጣ፤

ከመካከላቸውም ብርቱ ነን ባዮችን ገደለ፤

የእስራኤልንም አበባ ወጣቶች ቀጠፈ።

32ይህም ሁሉ ሆኖ በበደላቸው ገፉበት፤

ድንቅ ሥራዎቹንም አላመኑም።

33ስለዚህ ዘመናቸውን በከንቱ፣

ዕድሜያቸውንም በድንጋጤ ጨረሰ።

34እርሱ በገደላቸው ጊዜ ፈለጉት፤

ከልባቸው በመሻትም ወደ እግዚአብሔር ተመለሱ።

35እግዚአብሔር ዐለታቸው፣

ልዑል አምላክ ቤዛቸው እንደ ሆነ ዐሰቡ።

36ነገር ግን በአፋቸው ሸነገሉት፤

በአንደበታቸው ዋሹት።

37ልባቸው በእርሱ የጸና አልነበረም፤

ለኪዳኑም ታማኞች አልነበሩም።

38እርሱ ግን መሓሪ እንደ መሆኑ፣

በደላቸውን ይቅር አለ፤

አላጠፋቸውም፤

ቍጣውን ብዙ ጊዜ ገታ፤

መዓቱንም ሁሉ አላወረደም።

39ወጥቶ የማይመለስ ነፋስ፣

ሥጋ ለባሾች መሆናቸውን ዐሰበ።

40በምድረ በዳ ስንት ጊዜ ዐመፁበት!

በበረሓስ ምን ያህል አሳዘኑት!

41ደግመው ደጋግመው እግዚአብሔርን ተፈታተኑት፤

የእስራኤልንም ቅዱስ አስቈጡት።

42እነርሱን በዚያን ቀን ከጠላት የታደገበትን፣

ያን ኀይሉን አላስታወሱም፤

43በግብፅ ያደረገውን ታምራዊ ምልክት፣

በጣኔዎስም በረሓ ያሳየውን ድንቅ ሥራ አላሰቡም።

44ወንዞቻቸውን ወደ ደም ለወጠ፤

ከጅረቶቻቸውም መጠጣት አልቻሉም።

45የዝንብ ሰራዊት ሰደደባቸው፤ ነደፏቸውም፤

ጓጕንቸርም ላከባቸው፤ ሰዎችንም አጠፉ።

46አዝመራቸውን ለኵብኵባ፣

ሰብላቸውንም ለአንበጣ ሰጠባቸው።

47የወይን ተክላቸውን በበረዶ፣

የበለስ ዛፋቸውንም በውርጭ አጠፋ።

48ከብቶቻቸውን ለበረዶ፣

የከብት መንጋቸውን ለመብረቅ እሳት ዳረገ።

49ጽኑ ቍጣውን በላያቸው ሰደደ፤

መዓቱን፣ የቅናቱን ቍጣና

መቅሠፍቱን ላከባቸው፤

አጥፊ የመላእክት ሰራዊትም ሰደደባቸው።

50ለቍጣው መንገድ አዘጋጀ፤

ነፍሳቸውንም ከሞት አላተረፈም፤

ነገር ግን ሕይወታቸውን ለመቅሠፍት አሳልፎ ሰጠ።

51የዐፍላ ጕልበታቸው መጀመሪያ የሆኑትን በካም ድንኳን፣

በኵሮቻቸውንም ሁሉ በግብፅ ምድር ፈጀ።

52ሕዝቡን ግን እንደ በግ አወጣቸው፤

በምድረ በዳም እንደ መንጋ መራቸው።

53በሰላም መራቸው፤ እነርሱም አልፈሩም፤

ጠላቶቻቸውን ግን ባሕር ዋጣቸው።

54ቀኝ እጁም ወዳስገኘችው ወደዚህ ተራራ፣

ወደ ቅድስት ምድር አገባቸው።

55ሕዝቦችን ከፊታቸው አባረረ፤

ምድራቸውን ርስት አድርጎ አከፋፈላቸው፤

የእስራኤልንም ነገዶች በጠላቶቻቸው ቤት አኖረ።

56እነርሱ ግን አምላክን ተፈታተኑት፤

በልዑልም ላይ ዐመፁ፤

ሥርዐቱንም አልጠበቁም።

57ተመልሰው እንደ አባቶቻቸው ከዳተኛ ሆኑ፤

እንደማያስተማምን ጠማማ ቀስት ተወላገዱ።

58በኰረብታ ማምለኪያዎቻቸው አስቈጡት፤

ተቀርጸው በተሠሩ ጣዖቶቻቸው አስቀኑት።

59እግዚአብሔር ይህን በሰማ ጊዜ እጅግ ተቈጣ፤

እስራኤልንም ፈጽሞ ተወ።

60በሰዎች መካከል ያቆማትን ድንኳን፣

የሴሎን ማደሪያ ተዋት።

61የኀይሉን ምልክት አስማረካት፤

ክብሩንም ለጠላቶቹ እጅ አሳልፎ ሰጠ።

62ሕዝቡን ለሰይፍ ዳረገ፤

በርስቱም ላይ እጅግ ተቈጣ።

63ጕልማሶቻቸውን እሳት በላቸው፤

ልጃገረዶቻቸውም የሰርግ ዘፈን አልተዘፈነላቸውም።

64ካህናታቸው በሰይፍ ተገደሉ፤

መበለቶቻቸውም ማልቀስ ተሳናቸው።

65ጌታም ከእንቅልፍ እንደሚነቃ ተነሣ፤

የወይን ጠጅ ስካር እንደ በረደለት ጀግናም ብድግ አለ።

66ጠላቶቹን መትቶ ወደ ኋላ መለሳቸው፤

የዘላለም ውርደትም አከናነባቸው።

67የዮሴፍን ድንኳን ተዋት፤

የኤፍሬምንም ነገድ አልመረጠም።

68ነገር ግን የይሁዳን ነገድ፣

የወደዳትን የጽዮንን ተራራ መረጠ።

69መቅደሱን እንደ ታላቅ ከፍታ፣

ለዘላለም እንደ መሠረታት ምድር ሠራት።

70ባሪያውን ዳዊትን መረጠ፤

ከበጎች ጕረኖ ውስጥ ወሰደው፤

71ለሕዝቡ ለያዕቆብ፣

ለርስቱም ለእስራኤል እረኛ ይሆን ዘንድ፣

የሚያጠቡ በጎችን ከመከተል አመጣው።

72እርሱም በቅን ልቡ ጠበቃቸው፤

ብልኀት በተሞላ እጁም መራቸው።

New International Version – UK

Psalms 78:1-72

Psalm 78

A maskilTitle: Probably a literary or musical term of Asaph.

1My people, hear my teaching;

listen to the words of my mouth.

2I will open my mouth with a parable;

I will utter hidden things, things from of old –

3things we have heard and known,

things our ancestors have told us.

4We will not hide them from their descendants;

we will tell the next generation

the praiseworthy deeds of the Lord,

his power, and the wonders he has done.

5He decreed statutes for Jacob

and established the law in Israel,

which he commanded our ancestors

to teach their children,

6so that the next generation would know them,

even the children yet to be born,

and they in turn would tell their children.

7Then they would put their trust in God

and would not forget his deeds

but would keep his commands.

8They would not be like their ancestors –

a stubborn and rebellious generation,

whose hearts were not loyal to God,

whose spirits were not faithful to him.

9The men of Ephraim, though armed with bows,

turned back on the day of battle;

10they did not keep God’s covenant

and refused to live by his law.

11They forgot what he had done,

the wonders he had shown them.

12He did miracles in the sight of their ancestors

in the land of Egypt, in the region of Zoan.

13He divided the sea and led them through;

he made the water stand up like a wall.

14He guided them with the cloud by day

and with light from the fire all night.

15He split the rocks in the wilderness

and gave them water as abundant as the seas;

16he brought streams out of a rocky crag

and made water flow down like rivers.

17But they continued to sin against him,

rebelling in the wilderness against the Most High.

18They wilfully put God to the test

by demanding the food they craved.

19They spoke against God;

they said, ‘Can God really

spread a table in the wilderness?

20True, he struck the rock,

and water gushed out,

streams flowed abundantly,

but can he also give us bread?

Can he supply meat for his people?’

21When the Lord heard them, he was furious;

his fire broke out against Jacob,

and his wrath rose against Israel,

22for they did not believe in God

or trust in his deliverance.

23Yet he gave a command to the skies above

and opened the doors of the heavens;

24he rained down manna for the people to eat,

he gave them the grain of heaven.

25Human beings ate the bread of angels;

he sent them all the food they could eat.

26He let loose the east wind from the heavens

and by his power made the south wind blow.

27He rained meat down on them like dust,

birds like sand on the seashore.

28He made them come down inside their camp,

all around their tents.

29They ate till they were gorged –

he had given them what they craved.

30But before they turned from what they craved,

even while the food was still in their mouths,

31God’s anger rose against them;

he put to death the sturdiest among them,

cutting down the young men of Israel.

32In spite of all this, they kept on sinning;

in spite of his wonders, they did not believe.

33So he ended their days in futility

and their years in terror.

34Whenever God slew them, they would seek him;

they eagerly turned to him again.

35They remembered that God was their Rock,

that God Most High was their Redeemer.

36But then they would flatter him with their mouths,

lying to him with their tongues;

37their hearts were not loyal to him,

they were not faithful to his covenant.

38Yet he was merciful;

he forgave their iniquities

and did not destroy them.

Time after time he restrained his anger

and did not stir up his full wrath.

39He remembered that they were but flesh,

a passing breeze that does not return.

40How often they rebelled against him in the wilderness

and grieved him in the wasteland!

41Again and again they put God to the test;

they vexed the Holy One of Israel.

42They did not remember his power –

the day he redeemed them from the oppressor,

43the day he displayed his signs in Egypt,

his wonders in the region of Zoan.

44He turned their river into blood;

they could not drink from their streams.

45He sent swarms of flies that devoured them,

and frogs that devastated them.

46He gave their crops to the grasshopper,

their produce to the locust.

47He destroyed their vines with hail

and their sycamore-figs with sleet.

48He gave over their cattle to the hail,

their livestock to bolts of lightning.

49He unleashed against them his hot anger,

his wrath, indignation and hostility –

a band of destroying angels.

50He prepared a path for his anger;

he did not spare them from death

but gave them over to the plague.

51He struck down all the firstborn of Egypt,

the firstfruits of manhood in the tents of Ham.

52But he brought his people out like a flock;

he led them like sheep through the wilderness.

53He guided them safely, so they were unafraid;

but the sea engulfed their enemies.

54And so he brought them to the border of his holy land,

to the hill country his right hand had taken.

55He drove out nations before them

and allotted their lands to them as an inheritance;

he settled the tribes of Israel in their homes.

56But they put God to the test

and rebelled against the Most High;

they did not keep his statutes.

57Like their ancestors they were disloyal and faithless,

as unreliable as a faulty bow.

58They angered him with their high places;

they aroused his jealousy with their idols.

59When God heard them, he was furious;

he rejected Israel completely.

60He abandoned the tabernacle of Shiloh,

the tent he had set up among humans.

61He sent the ark of his might into captivity,

his splendour into the hands of the enemy.

62He gave his people over to the sword;

he was furious with his inheritance.

63Fire consumed their young men,

and their young women had no wedding songs;

64their priests were put to the sword,

and their widows could not weep.

65Then the Lord awoke as from sleep,

as a warrior wakes from the stupor of wine.

66He beat back his enemies;

he put them to everlasting shame.

67Then he rejected the tents of Joseph,

he did not choose the tribe of Ephraim;

68but he chose the tribe of Judah,

Mount Zion, which he loved.

69He built his sanctuary like the heights,

like the earth that he established for ever.

70He chose David his servant

and took him from the sheepfolds;

71from tending the sheep he brought him

to be the shepherd of his people Jacob,

of Israel his inheritance.

72And David shepherded them with integrity of heart;

with skilful hands he led them.