መዝሙር 74 – NASV & NIVUK

New Amharic Standard Version

መዝሙር 74:1-23

መዝሙር 74

ስለ መቅደሱ መፍረስ የቀረበ ጸሎት

የአሳፍ ትምህርት።

1አምላክ ሆይ፤ ለዘላለም የጣልኸን ለምንድን ነው?

በማሰማሪያህ ባሉ በጎችህስ ላይ ቍጣህ ለምን ነደደ?

2ጥንት ገንዘብህ ያደረግሃትን ጉባኤ፣

የዋጀሃትን የርስትህን ነገድ፣

መኖሪያህ ያደረግሃትን የጽዮን ተራራ ዐስብ።

3ርምጃህን ለዘላለሙ ባድማ ወደ ሆነው አቅና፤

ጠላት በመቅደስህ ውስጥ ያለውን ሁሉ አበላሽቷል።

4ጠላቶችህ በመገናኛ ስፍራህ መካከል ደነፉ፤

አርማቸውንም ምልክት አድርገው በዚያ አቆሙ።

5በጫካ መካከል ዛፎችን ለመቍረጥ፣

መጥረቢያ የሚያነሣ ሰው መሰሉ።

6በእደ ጥበብ ያጌጠውን ሥራ ሁሉ፣

በመጥረቢያና በመዶሻ ሰባበሩት።

7መቅደስህን አቃጥለው አወደሙት፤

የስምህንም ማደሪያ አረከሱ።

8በልባቸውም፣ “ፈጽሞ እንጨቍናቸዋለን” አሉ፤

እግዚአብሔር በምድሪቱ ላይ የተመለከበትን ስፍራ ሁሉ አቃጠሉ።

9የምናየው ምልክት የለም፤

ከእንግዲህ የሚነሣ አንድም ነቢይ የለም፤

ይህ እስከ መቼ እንደሚቀጥል የሚያውቅ በእኛ ዘንድ የለም።

10አምላክ ሆይ፤ ጠላት የሚያሾፈው እስከ መቼ ነው?

ባላንጣስ ለዘላለም በስምህ ያላግጣልን?

11እጅህን ለምን ትሰበስባለህ?

ቀኝ እጅህን ለምን በብብትህ ሥር ታቈያለህ?

12አምላክ ሆይ፤ አንተ ከጥንት ጀምሮ ንጉሤ ነህ፤

በምድር ላይ ማዳንን አደረግህ።

13ባሕርን በኀይልህ የከፈልህ አንተ ነህ፤

የባሕሩንም አውሬ ራሶች በውሃ ውስጥ ቀጠቀጥህ።

14የሌዋታንን ራሶች አደቀቅህ፤

ለምድረ በዳ ፍጥረታትም ምግብ አድርገህ የሰጠሃቸው፣

15ምንጮችንና ፈሳሾችን ያፈለቅህ አንተ ነህ፤

ሳያቋርጡ የሚፈስሱትንም ወንዞች አደረቅህ።

16ቀኑ የአንተ ነው፤ ሌሊቱም የአንተ ነው፤

ጨረቃንና ፀሓይን አንተ አጸናሃቸው።

17የምድርን ዳርቻ ሁሉ የወሰንህ አንተ ነህ፤

በጋውንም ክረምቱንም አንተ ሠራህ።

18እግዚአብሔር ሆይ፤ ጠላት እንዴት እንደሚያሾፍ፣

ከንቱ ሕዝብም ስምህን እንዴት እንዳቃለለ ዐስብ።

19የርግብህን ነፍስ አሳልፈህ ለዱር አራዊት አትስጥ፤

የችግረኞች ሕዝብህን ሕይወት ለዘላለሙ አትርሳ።

20ኪዳንህን ዐስብ፤

የዐመፅ መናኸሪያ በምድሪቱ ጨለማ ስፍራዎች ሞልተዋልና።

21የተጨቈኑት ዐፍረው አይመለሱ፤

ድኾችና ችግረኞች ስምህን ያመስግኑ።

22አምላክ ሆይ፤ ተነሥ፤ ለዐላማህ ተሟገት፤

ከንቱ ሰው ቀኑን ሙሉ እንደሚያላግጥብህ ዐስብ።

23የባላጋራዎችህን ድንፋታ፣

ዘወትር የሚነሣውን የጠላቶችህን ፉከራ አትርሳ።

New International Version – UK

Psalms 74:1-23

Psalm 74

A maskilTitle: Probably a literary or musical term of Asaph.

1O God, why have you rejected us for ever?

Why does your anger smoulder against the sheep of your pasture?

2Remember the nation you purchased long ago,

the people of your inheritance, whom you redeemed –

Mount Zion, where you dwelt.

3Turn your steps towards these everlasting ruins,

all this destruction the enemy has brought on the sanctuary.

4Your foes roared in the place where you met with us;

they set up their standards as signs.

5They behaved like men wielding axes

to cut through a thicket of trees.

6They smashed all the carved panelling

with their axes and hatchets.

7They burned your sanctuary to the ground;

they defiled the dwelling-place of your Name.

8They said in their hearts, ‘We will crush them completely!’

They burned every place where God was worshipped in the land.

9We are given no signs from God;

no prophets are left,

and none of us knows how long this will be.

10How long will the enemy mock you, God?

Will the foe revile your name for ever?

11Why do you hold back your hand, your right hand?

Take it from the folds of your garment and destroy them!

12But God is my King from long ago;

he brings salvation on the earth.

13It was you who split open the sea by your power;

you broke the heads of the monster in the waters.

14It was you who crushed the heads of Leviathan

and gave it as food to the creatures of the desert.

15It was you who opened up springs and streams;

you dried up the ever-flowing rivers.

16The day is yours, and yours also the night;

you established the sun and moon.

17It was you who set all the boundaries of the earth;

you made both summer and winter.

18Remember how the enemy has mocked you, Lord,

how foolish people have reviled your name.

19Do not hand over the life of your dove to wild beasts;

do not forget the lives of your afflicted people for ever.

20Have regard for your covenant,

because haunts of violence fill the dark places of the land.

21Do not let the oppressed retreat in disgrace;

may the poor and needy praise your name.

22Rise up, O God, and defend your cause;

remember how fools mock you all day long.

23Do not ignore the clamour of your adversaries,

the uproar of your enemies, which rises continually.