መዝሙር 62 – NASV & PCB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 62:1-12

መዝሙር 62

ተስፋ በእግዚአብሔር ላይ ብቻ

ለመዘምራን አለቃ፤ ለኤዶታም፤ የዳዊት መዝሙር።

1ነፍሴ ዕረፍት የምታገኘው በእግዚአብሔር ብቻ ነው፤

ድነቴም የሚመጣልኝ ከእርሱ ዘንድ ነው።

2ዐለቴና መድኀኒቴ እርሱ ብቻ ነው፤

መጠጊያዬም እርሱ ነው፤ ከቶም አልናወጥም።

3ሰውን የምታጠቁት እስከ መቼ ነው?

ይህን የዘመመ ግድግዳ፣ የተንጋደደ ዐጥር፣

ሁላችሁ ገፍታችሁ ልትጥሉት ትሻላችሁ?

4ከታላቅ ክብሩ ሊያዋርዱት፣

ይህን አንድ ነገር ወጠኑ፤

ሐሰት ባለበት ነገር ደስ ይሰኛሉ፤

በአፋቸው ይመርቃሉ፤

በልባቸው ግን ይራገማሉ። ሴላ

5ነፍሴ ሆይ፤ ዐርፈሽ እግዚአብሔርን ብቻ ጠብቂ፤

ተስፋዬ ከእርሱ ዘንድ ነውና።

6ዐለቴና መድኀኒቴ እርሱ ብቻ ነው፤

መጠጊያዬም እርሱ ነው፤ እኔም አልናወጥም።

7መዳኔና ክብሬ በእግዚአብሔር ነው፤62፥7 ወይም ልዑል እግዚአብሔር ድነቴና ክብሬ ነው ተብሎ መተርጐም ይችላል።

ብርቱ ዐለቴና መሸሸጊያዬ በእግዚአብሔር ነው።

8ሰዎች ሆይ፤ ሁልጊዜ በእርሱ ታመኑ፤

ልባችሁን በፊቱ አፍስሱ፤

እግዚአብሔር መጠጊያችን ነውና። ሴላ

9ከተናቀ ወገን መወለድ ከንቱ፣

ከከበረውም መወለድ ሐሰት ነው።

በሚዛን ላይ ከፍ ብለው ቢታዩም፣

ሁሉም በአንድነት ከነፋስ የቀለሉ ናቸው።

10በዝርፊያ አትታመኑ፤

በቅሚያም ተስፋ አታድርጉ፤

በዚህ ብትበለጽጉም፣

ልባችሁ ይህን አለኝታ አያድርግ።

11እግዚአብሔር አንድ ነገር ተናገረ፤

እኔም ይህን ሁለት ጊዜ ሰማሁ፤

ኀይል የእግዚአብሔር ነው።

12ጌታ ሆይ፤ ምሕረትም የአንተ ነው፤

አንተ ለእያንዳንዱ፣

እንደ ሥራው ትከፍለዋለህ።

Persian Contemporary Bible

مزامير 62:1-12

اعتماد به محافظت خدا

1جان من تنها نزد خدا آرام می‌يابد، زيرا نجات من از جانب اوست. 2او نجات دهنده و تنها صخرهٔ پناهگاه من است؛ او قلعهٔ محافظ من است، پس هرگز شكست نخواهم خورد.

3ای آدميان، تا به كی هجوم می‌آوريد تا مرا كه همچون ديواری فرو ريخته‌ام از پای درآوريد؟ 4تنها فكرتان اين است كه مرا از اين مقامی كه دارم به زير اندازيد؛ شما دروغ را دوست داريد. به زبان خود مرا بركت می‌دهيد ولی در دلتان لعنتم می‌كنيد.

5ای جان من، تنها نزد خدا آرام ياب، زيرا اميد من بر اوست. 6او نجات دهنده و تنها صخرهٔ پناهگاه من است؛ او قلعهٔ محافظ من است، پس هرگز شكست نخواهم خورد. 7نجات و عزت من از جانب خداست؛ قوت و پناهگاه من خداست. 8ای مردم، همه وقت بر او توكل نماييد؛ دلهای خود را به حضور او بريزيد، زيرا خدا پناهگاه ماست.

9همهٔ انسانها در مقابل او ناچيزند؛ اشخاص سرشناس و افراد بی‌نام و نشان، همگی در ترازوی او بالا می‌روند، زيرا از باد هم سبكترند. 10بر خشونت تكيه نكنيد و به كسب ثروت از راه دزدی دل خوش نكنيد، و هرگاه ثروتتان زياد شود دل بر آن نبنديد.

11بيش از يک بار شنيده‌ام كه خداوند فرموده است: «قوت از آن من است.» 12ای خداوند، رحمت نيز از آن توست، و تو هر کس را بر اساس كارهايش پاداش خواهی داد.