መዝሙር 61 – NASV & NIV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 61:1-8

መዝሙር 61

የግዞተኛ ጸሎት

ለመዘምራን አለቃ፤ በበገናዎች የሚዘመር፤ የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ ጩኸቴን ስማ፤

ጸሎቴንም አድምጥ።

2ልቤ በዛለ ጊዜ፣

ከምድር ዳርቻ ወደ አንተ እጣራለሁ፤

ከእኔ ይልቅ ከፍ ወዳለው ዐለት ምራኝ።

3አንተ መጠጊያዬ፣

ከጠላትም የምተገንብህ ጽኑ ግንብ ሆነኸኛልና።

4በድንኳንህ ለዘላለም ልኑር፤

በክንፎችህም ጥላ ልከለል። ሴላ

5አምላክ ሆይ፤ ስእለቴን ሰምተሃልና፤

ስምህን የሚፈሩትንም ሰዎች ርስት ለእኔ ሰጠህ።

6የንጉሡን ዕድሜ አርዝምለት፤

ዘመኑንም እስከ ብዙ ትውልድ ጨምርለት፤

7በእግዚአብሔር ፊት ለዘላለም ይንገሥ፤

ይጠብቁት ዘንድ ምሕረትህንና ታማኝነትህን አዘጋጅለት።

8ስለዚህ ለስምህ ዘወትር ውዳሴ አቀርባለሁ፤

ስእለቴንም በየጊዜው እፈጽማለሁ።

New International Version

Psalms 61:1-8

Psalm 61In Hebrew texts 61:1-8 is numbered 61:2-9.

For the director of music. With stringed instruments. Of David.

1Hear my cry, O God;

listen to my prayer.

2From the ends of the earth I call to you,

I call as my heart grows faint;

lead me to the rock that is higher than I.

3For you have been my refuge,

a strong tower against the foe.

4I long to dwell in your tent forever

and take refuge in the shelter of your wings.61:4 The Hebrew has Selah (a word of uncertain meaning) here.

5For you, God, have heard my vows;

you have given me the heritage of those who fear your name.

6Increase the days of the king’s life,

his years for many generations.

7May he be enthroned in God’s presence forever;

appoint your love and faithfulness to protect him.

8Then I will ever sing in praise of your name

and fulfill my vows day after day.