መዝሙር 60 – NASV & NSP

New Amharic Standard Version

መዝሙር 60:1-12

መዝሙር 60

ከሽንፈት በኋላ የቀረበ ብሔራዊ ጸሎት

60፥5-12 ተጓ ምብ – መዝ 108፥6-13

ለመዘምራን አለቃ፤ “የኪዳን ጽጌረዳ” በሚለው ቅኝት የሚዘመር፤60 ርእሱ የሥነ ጽሑፉን ቅርጽ ወይም የመዝሙሩን ሁኔታ የሚያሳይ ሊሆን ይችላል። በሰሜናዊ ምዕራብ መስጴጦምያና60 ርእሱ የአራማውያን ወይም የሰሜን ምዕራብ መስጴጦምያ ነው። በማእከላዊ ሶርያ የሚኖሩትን አራማውያን60 ርእሱ በመካከለኛው ሶርያ የሚገኙት አራማውያንን የሚያመለክት ነው። በወጋቸው ጊዜ፣ ኢዮአብም ተመልሶ በጨው ሸለቆ ዐሥራ ሁለት ሺሕ ኤዶማውያንን በፈጀ ጊዜ፣ ለትምህርት፤ የዳዊት ቅኔ።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ ጣልኸን፤ አንኰታኰትኸን፤

ተቈጣኸንም፤ አሁን ግን መልሰህ አብጀን።

2ምድሪቱን አናወጥሃት፤ ፍርክስክስ አደረግሃት፤

ትንገዳገዳለችና ስብራቷን ጠግን።

3ለሕዝብህ አበሳውን አሳየኸው፤

ናላ የሚያዞር የወይን ጠጅ እንድንጠጣም ሰጠኸን።

4ነገር ግን ከቀስት እንዲያመልጡ፣

ለሚፈሩህ ምልክት አቆምህላቸው። ሴላ

5ወዳጆችህ ይድኑ ዘንድ፣

በቀኝ እጅህ ርዳን፤ መልስም ስጠን።

6እግዚአብሔር ከመቅደሱ እንዲህ ሲል ተናገረ፤

“ደስ እያለኝ የሴኬምን ምድር እሸነሽናለሁ፤

የሱኮትን ሸለቆ አከፋፍላለሁ።

7ገለዓድ የእኔ ነው፤ ምናሴም የእኔ ነው፤

ኤፍሬም የራስ ቍሬ ነው፤

ይሁዳም በትረ መንግሥቴ ነው።

8ሞዓብ የመታጠቢያ ገንዳዬ ነው፤

በኤዶምያስ ላይ ጫማዬን እወረውራለሁ፤

በፍልስጥኤም ላይ በድል እልል እላለሁ።”

9ወደ ተመሸገው ከተማ ማን ያመጣኛል?

ማንስ ወደ ኤዶምያስ ይመራኛል?

10አምላክ ሆይ፤ የጣልኸን አንተ አይደለህምን?

እግዚአብሔር ሆይ፤ ከሰራዊታችን ጋር እኮ አልወጣ አልህ!

11በጠላት ላይ ድልን አቀዳጀን፤

የሰው ርዳታ ከንቱ ነውና።

12በእግዚአብሔር ክንደ ብርቱ እንሆናለን፤

ጠላቶቻችንን የሚረጋግጥልን እርሱ ነውና።

New Serbian Translation

Псалми 60:1-12

Псалам 60

Хоровођи. Према „Љиљанима“. Сведочења. Давидова песма поуздања у Бога. За поуку: када се борио против Арам-Нахарајима и Арам-Сове и када се Јоав вратио, па у Сланој долини побио дванаест хиљада Едомаца.

1Одбацио си нас, Боже,

срушио нас, разгневио се.

Опорави нас!

2Ти си земљу уздрмао,

расцепао си је;

раселине њене споји

јер је уздрмана.

3Пустио си да твој народ види страхоту,

приморао да пијемо вино што опија.

4Заставу си богобојазнима дао

да се због истине60,4 Или: због лука. развије. Села

5Десницом нас својом спаси, услиши нас,

па да твоји миљеници избављени буду.

6У свом Светилишту Бог је објавио:

„Заклицаћу, поделићу Сихем,

премерићу долину Сокота.

7Мој је Галад, мој је Манасија;

Јефрем ми је кацига на глави,

а Јуда ми царско жезло.

8Моав ми је корито за прање,

на Едом сам бацио сандалу;

Филистејо, због мене ускликни!“

9Ко ће мене да отпрати у град утврђени?

А на Едом ко ће ме повести?

10Нећеш ли ти, о, Боже,

који си нас одбацио,

па с војскама нашим, Боже,

више не корачаш?

11Помоћ дај нам испред противника,

узалуд је људско избављење.

12Силно ћемо ступати са Богом,

изгазиће наше противнике!