መዝሙር 60 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 60:1-12

መዝሙር 60

ከሽንፈት በኋላ የቀረበ ብሔራዊ ጸሎት

60፥5-12 ተጓ ምብ – መዝ 108፥6-13

ለመዘምራን አለቃ፤ “የኪዳን ጽጌረዳ” በሚለው ቅኝት የሚዘመር፤60 ርእሱ የሥነ ጽሑፉን ቅርጽ ወይም የመዝሙሩን ሁኔታ የሚያሳይ ሊሆን ይችላል። በሰሜናዊ ምዕራብ መስጴጦምያና60 ርእሱ የአራማውያን ወይም የሰሜን ምዕራብ መስጴጦምያ ነው። በማእከላዊ ሶርያ የሚኖሩትን አራማውያን60 ርእሱ በመካከለኛው ሶርያ የሚገኙት አራማውያንን የሚያመለክት ነው። በወጋቸው ጊዜ፣ ኢዮአብም ተመልሶ በጨው ሸለቆ ዐሥራ ሁለት ሺሕ ኤዶማውያንን በፈጀ ጊዜ፣ ለትምህርት፤ የዳዊት ቅኔ።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ ጣልኸን፤ አንኰታኰትኸን፤

ተቈጣኸንም፤ አሁን ግን መልሰህ አብጀን።

2ምድሪቱን አናወጥሃት፤ ፍርክስክስ አደረግሃት፤

ትንገዳገዳለችና ስብራቷን ጠግን።

3ለሕዝብህ አበሳውን አሳየኸው፤

ናላ የሚያዞር የወይን ጠጅ እንድንጠጣም ሰጠኸን።

4ነገር ግን ከቀስት እንዲያመልጡ፣

ለሚፈሩህ ምልክት አቆምህላቸው። ሴላ

5ወዳጆችህ ይድኑ ዘንድ፣

በቀኝ እጅህ ርዳን፤ መልስም ስጠን።

6እግዚአብሔር ከመቅደሱ እንዲህ ሲል ተናገረ፤

“ደስ እያለኝ የሴኬምን ምድር እሸነሽናለሁ፤

የሱኮትን ሸለቆ አከፋፍላለሁ።

7ገለዓድ የእኔ ነው፤ ምናሴም የእኔ ነው፤

ኤፍሬም የራስ ቍሬ ነው፤

ይሁዳም በትረ መንግሥቴ ነው።

8ሞዓብ የመታጠቢያ ገንዳዬ ነው፤

በኤዶምያስ ላይ ጫማዬን እወረውራለሁ፤

በፍልስጥኤም ላይ በድል እልል እላለሁ።”

9ወደ ተመሸገው ከተማ ማን ያመጣኛል?

ማንስ ወደ ኤዶምያስ ይመራኛል?

10አምላክ ሆይ፤ የጣልኸን አንተ አይደለህምን?

እግዚአብሔር ሆይ፤ ከሰራዊታችን ጋር እኮ አልወጣ አልህ!

11በጠላት ላይ ድልን አቀዳጀን፤

የሰው ርዳታ ከንቱ ነውና።

12በእግዚአብሔር ክንደ ብርቱ እንሆናለን፤

ጠላቶቻችንን የሚረጋግጥልን እርሱ ነውና።

Ketab El Hayat

مزمور 60:1-12

الْمَزْمُورُ السِّتُّونَ

لِقَائِدِ الْمُنْشِدِينَ عَلَى السُّوسَنِّ. شَهَادَةٌ مُذَهَّبَةٌ لِدَاوُدَ لِلتَّعْلِيمِ لَمَّا حَارَبَ سُورِيِّي مَا بَيْنَ النَّهْرَيْنِ وَسُورِيِّي صُوبَةَ، فَرَجَعَ يُوآبُ وَصَرَعَ مِنَ الأَدُومِيِّينَ فِي وَادِي الْمِلْحِ اثْنَيْ عَشَرَ أَلْفاً.

1يَا اللهُ قَدْ رَذَلْتَنَا، وَبَدَّدْتَنَا وَسَخِطْتَ عَلَيْنَا، فَرُدَّنَا إِلَيْكَ. 2زَلْزَلْتَ الأَرْضَ وَصَدَّعْتَهَا، فَاجْبُرْ كَسْرَهَا لأَنَّهَا تَهْتَزُّ. 3جَعَلْتَ شَعْبَكَ يُعَانِي الْمَشَقَّاتِ. وَتَرَنَّحْنَا تَحْتَ وَقْعِ ضَرَبَاتِكَ كَالسُّكَارَى. 4أَعْطَيْتَ خَائِفِيكَ رَايَةً تُرْفَعُ لأَجْلِ الْحَقِّ. 5لِكَيْ يَنْجُوَ أَحِبَّاؤُكَ. خَلِّصْ بِيَمِينِكَ وَاسْتَجِبْ لِي.

6قَدْ تَكَلَّمَ اللهُ فِي قَدَاسَتِهِ، لِذَلِكَ أَبْتَهِجُ وَأَقْسِمُ أَرْضَ شَكِيمَ وَأَقِيسُ وَادِي سُكُّوتَ، 7لِي جِلْعَادُ، وَلِي مَنَسَّى. أَفْرَايِمُ خُوذَةُ رَأْسِي، وَيَهُوذَا صَوْلَجَانِي. 8مُوآبُ مِرْحَضَتِي، وَعَلَى أَدُومَ أُلْقِي حِذَائِي، وَعَلَى فَلَسْطِينَ أَهْتِفُ مُنْتَصِراً.

9مَنْ يَقُودُنِي لِمُحَارَبَةِ الْمَدِينَةِ الْمُحَصَّنَةِ؟ مَنْ يَهْدِينِي إِلَى أَدُومَ؟ 10أَلَيْسَ أَنْتَ يَا اللهُ الَّذِي أَقْصَيْتَنَا وَلَمْ تَعُدْ تَخْرُجُ مَعَ جُيُوشِنَا؟ 11هَبْ لَنَا عَوْناً فِي الضِّيقِ، فَعَبَثٌ هُوَ خَلاصُ الإِنْسَانِ. 12بِعَوْنِ اللهِ نُحَارِبُ بِبَأْسٍ، وَهُوَ الَّذِي يَدُوسُ أَعْدَاءَنَا.