መዝሙር 58
የምድር ዳኞች ፈራጅ
ለመዘምራን አለቃ፤ “አታጥፋ” በሚለው ቅኝት የሚዘመር፤ የዳዊት ቅኔ58 ርእሱ የሥነ ጽሑፉን ቅርጽ ወይም የመዝሙሩን ሁኔታ የሚያሳይ ሊሆን ይችላል።።
1ኀያላን ሆይ፤ በውኑ ጽድቅ ከአፋችሁ ይወጣል?
የሰው ልጆች ሆይ፤ በቅን ትፈርዳላችሁን?
2የለም፤ በልባችሁ ክፋትን ታውጠነጥናላችሁ፤
በእጃችሁም ዐመፅን በምድር ላይ ትጐነጕናላችሁ።
3ክፉዎች በማሕፀን ሳሉ ከመንገድ የወጡ ናቸው፤
ሲወለዱ ጀምሮ የተሳሳቱና ውሸታሞች ናቸው።
4መርዛቸው እንደ እባብ መርዝ ነው፤
አልሰማ ብላ ጆሮዋን እንደ ደፈነች እፉኝት ናቸው፤
5ጆሮዋንም የደፈነችው የመተተኛውን
ወይም የጠቢቡን ደጋሚ ቃል ላለመስማት ነው።
6አምላክ ሆይ፤ ጥርሳቸውን በአፋቸው ውስጥ ስበር፤
እግዚአብሔር ሆይ፤ የአንበሶቹን መንጋጋ አወላልቅ!
7ፈጥኖ እንደሚያልፍ ወራጅ ውሃ ይጥፉ፤
ቀስታቸውን ሲስቡ ፍላጻቸው ዱልዱም ይሁን።
8ሲሄድ እንደሚቀልጥ ቀንድ አውጣ ይሁኑ፤
ፀሓይን እንደማያይ ጭንጋፍ ይሁኑ።
9የእሾኽ እሳት ገና ድስታችሁን ሳያሰማው፣
ርጥቡንም ደረቁንም እኩል በዐውሎ ነፋስ ጠራርጎ ይወስዳቸዋል።58፥9 በዕብራይስጡ የዚህ ሐረግ ትርጕም በትክክል አይታወቅም።
10ጻድቃን በቀልን ባዩ ጊዜ ደስ ይላቸዋል፤
እግራቸውንም በግፈኞች ደም ይታጠባሉ።
11ሰዎችም፣ “በርግጥ ለጻድቃን ብድራት ተቀምጦላቸዋል፤
በእውነትም በምድር ላይ የሚፈርድ አምላክ አለ” ይላሉ።
Salmo 58
Al director musical. Sígase la tonada de «No destruyas». Mictam de David.
1¿Acaso vosotros, gobernantes, actuáis con justicia,
y juzgáis con rectitud a los seres humanos?
2Al contrario, con la mente tramáis injusticia,
y la violencia de vuestras manos se desata en el país.
3Los malvados se pervierten desde que nacen;
desde el vientre materno se desvían los mentirosos.
4Su veneno es como el de las serpientes,
como el de una cobra que se hace la sorda
5para no escuchar la música del mago,
del diestro en encantamientos.
6Rómpeles, oh Dios, los dientes;
¡arráncales, Señor, los colmillos a esos leones!
7Que se escurran, como el agua entre los dedos;
que se rompan sus flechas al tensar el arco.
8Que se disuelvan, como babosa rastrera;
que no vean la luz, cual si fueran abortos.
9Que, sin darse cuenta, ardan como espinos;
que el viento los arrastre, estén verdes o secos.
10Se alegrará el justo al ver la venganza,
al empapar sus pies en la sangre del impío.
11Dirá entonces la gente:
«Ciertamente los justos son recompensados;
ciertamente hay un Dios que juzga en la tierra».