መዝሙር 57 – NASV & NIV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 57:1-11

መዝሙር 57

በጨካኝ ጠላቶች ዘንድ

57፥7-11 ተጓ ምብ – መዝ 108፥1-5

ለመዘምራን አለቃ፤ “አታጥፋ” በሚለው ቅኝት የሚዘመር፤ ከሳኦል ፊት ሸሽቶ በዋሻ በነበረበት ጊዜ፤ የዳዊት ቅኔ57 ርእሱ የሥነ ጽሑፉን ቅርጽ ወይም የመዝሙሩን ሁኔታ የሚያሳይ ሊሆን ይችላል።

1ማረኝ፤ እግዚአብሔር ሆይ፤ ማረኝ፤

ነፍሴ አንተን መጠጊያ አድርጋለችና፤

በክንፎችህ ሥር እጠለላለሁ።

2ለእኔ ያሰበውን ወደሚፈጽምልኝ አምላክ፣

ወደ ልዑል እግዚአብሔር እጮኻለሁ።

3ከሰማይ ልኮ ያድነኛል፤

የረገጡኝን ያዋርዳቸዋል፤ ሴላ

እግዚአብሔር ምሕረቱንና ታማኝነቱን ይልካል።

4ነፍሴ በአንበሶች ተከብባለች፤

በሚዘነጣጥሉ አራዊት መካከል ወድቄአለሁ፤

እነዚህም፣ ጥርሳቸው ጦርና ፍላጻ፣

ምላሳቸውም የተሳለ ሰይፍ የሆኑ ሰዎች ናቸው።

5እግዚአብሔር ሆይ፤ ከሰማያት በላይ ከፍ ከፍ በል፤

ክብርህም በምድር ሁሉ ላይ ትስፈን።

6ለእግሬ ወጥመድን ዘረጉ፤

ነፍሴንም አጐበጧት፤

በመተላለፊያዬ ላይ ጕድጓድ ቈፈሩ፤

ነገር ግን ራሳቸው ገቡበት። ሴላ

7እግዚአብሔር ሆይ፤ ልቤ ጽኑ ነው፤

ልቤ ጽኑ ነው፤

እቀኛለሁ፤ አዜማለሁ።

8ነፍሴ ሆይ፤ ንቂ!

በገናና መሰንቆም ተነሡ

እኔም በማለዳ እነሣለሁ።

9ጌታ ሆይ፤ በሕዝቦች መካከል አመሰግንሃለሁ፤

በሰዎችም መካከል እዘምርልሃለሁ፤

10ምሕረትህ እስከ ሰማያት ከፍ ብላለችና፤

ታማኝነትህም እስከ ደመናት ትደርሳለች።

11እግዚአብሔር ሆይ፤ ከሰማያት በላይ ከፍ ከፍ በል፤

ክብርህም በምድር ሁሉ ላይ ትስፈን።

New International Version

Psalms 57:1-11

Psalm 57In Hebrew texts 57:1-11 is numbered 57:2-12.

For the director of music. To the tune of “Do Not Destroy.” Of David. A miktam.Title: Probably a literary or musical term When he had fled from Saul into the cave.

1Have mercy on me, my God, have mercy on me,

for in you I take refuge.

I will take refuge in the shadow of your wings

until the disaster has passed.

2I cry out to God Most High,

to God, who vindicates me.

3He sends from heaven and saves me,

rebuking those who hotly pursue me—57:3 The Hebrew has Selah (a word of uncertain meaning) here and at the end of verse 6.

God sends forth his love and his faithfulness.

4I am in the midst of lions;

I am forced to dwell among ravenous beasts—

men whose teeth are spears and arrows,

whose tongues are sharp swords.

5Be exalted, O God, above the heavens;

let your glory be over all the earth.

6They spread a net for my feet—

I was bowed down in distress.

They dug a pit in my path—

but they have fallen into it themselves.

7My heart, O God, is steadfast,

my heart is steadfast;

I will sing and make music.

8Awake, my soul!

Awake, harp and lyre!

I will awaken the dawn.

9I will praise you, Lord, among the nations;

I will sing of you among the peoples.

10For great is your love, reaching to the heavens;

your faithfulness reaches to the skies.

11Be exalted, O God, above the heavens;

let your glory be over all the earth.