መዝሙር 55 – NASV & CARS

New Amharic Standard Version

መዝሙር 55:1-23

መዝሙር 55

በስደት ጊዜ የቀረበ ጸሎት

ለመዘምራን አለቃ፤ በበገናዎች፤ የዳዊት ትምህርት55 ርእሱ የሥነ ጽሑፉን ቅርጽ ወይም የመዝሙሩን ሁኔታ የሚያሳይ ሊሆን ይችላል።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ ጸሎቴን ስማ፤

ልመናዬን ቸል አትበል፤

2ወደ እኔ ተመልከት፤ መልስልኝም።

በውስጤ ታውኬአለሁ፤ ተናውጬአለሁም፤

3በጠላት ድምፅ ተሸበርሁ፤

በክፉዎች ድንፋታ ደነገጥሁ፤

መከራ አምጥተውብኛልና፤

በቍጣም ተነሣሥተው ጠላት ሆነውብኛል።

4ልቤ በውስጤ ተጨነቀብኝ፤

የሞት ድንጋጤም በላዬ መጣ።

5ፍርሀትና እንቅጥቃጤ መጣብኝ፤

ሽብርም ዋጠኝ።

6እኔም እንዲህ አልሁ፤ “ምነው የርግብ ክንፍ በኖረኝ!

በርሬ በሄድሁና ባረፍሁ ነበር፤

7እነሆ፤ ኰብልዬ በራቅሁ፣

በምድረ በዳም በሰነበትሁ ነበር፤ ሴላ

8ከዐውሎ ነፋስና ከውሽንፍር ሸሽቼ፣

ወደ መጠለያዬ ፈጥኜ በደረስሁ ነበር።”

9ጌታ ሆይ፤ ግፍንና ሁከትን በከተማዪቱ ውስጥ አይቼአለሁና፣

ግራ አጋባቸው፤ ቋንቋቸውንም ደበላልቅ።

10ቀንና ሌሊት ቅጥሯ ላይ ወጥተው ይዞሯታል፤

ተንኰልና መከራ በውስጧ አለ።

11ጥፋት በመካከሏ ይገኛል፤

ግፍና አታላይነትም ከጎዳናዋ አይጠፋም።

12የሚዘልፈኝ ጠላት አይደለምና፤

ቢሆንማ ኖሮ በታገሥሁት ነበር፤

የሚጠላኝ፣ ራሱንም ቀና ቀና ያደረገብኝ ባላንጣ አይደለም፤

ቢሆንማ ከእርሱ በተሸሸግሁ ነበር።

13ነገር ግን አድራጊው አንተ ነህ፤ እኩያዬ፣ ባልንጀራዬና ወዳጄ፤

14በእግዚአብሔርም ቤት አብረን በሕዝብ መካከል ተመላለስን፤

ደስ የሚል ፍቅር በአንድነት ነበረን።

15ሞት ሳይታሰብ ድንገት ይምጣባቸው፤

በሕይወት ሳሉ ወደ ሲኦል55፥15 ዕብራይስጡ ሲኦል ይላል፤ አንዳንድ የእንግሊዝኛ ቅጆች ግን መቃብር ይላሉ። ይውረዱ፤

ክፋት በመካከላቸው ዐድራለችና።

16እኔ ግን ወደ እግዚአብሔር እጣራለሁ፤

እግዚአብሔርም ያድነኛል።

17በማታ፣ በጧትና በቀትር፣

እጮኻለሁ፤ እቃትታለሁም፤

እርሱም ድምፄን ይሰማል።

18በተቃውሞ የተነሡብኝ ብዙዎች ናቸውና፣

ከተቃጣብኝ ጦርነት፣

ነፍሴን በሰላም ይቤዣታል።

19አካሄዳቸውን አልቀየሩምና፣

እግዚአብሔርንም አልፈሩትምና፣

ከጥንት ጀምሮ በዙፋኑ ላይ ያለ አምላክ፣ ሴላ

ሰምቶ ያዋርዳቸዋል።

20ባልንጀራዬ የምለው ሰው እጁን

በወዳጆቹ ላይ ሰነዘረ፤

ቃል ኪዳኑንም አፈረሰ።

21አፉ ከቅቤ ይልቅ የለዘበ ነው፤

በልቡ ግን ጦርነት አለ፤

ቃሉ ከዘይት ይልቅ የለሰለሰ ነው፤

ይሁን እንጂ የተመዘዘ ሰይፍ ነው።

22የከበደህን ነገር በእግዚአብሔር ላይ ጣል፤

እርሱ ደግፎ ይይዝሃል፤

የጻድቁንም መናወጥ ከቶ አይፈቅድም።

23አንተ ግን፣ እግዚአብሔር ሆይ፤ ክፉዎችን ወደ ጥፋት ጕድጓድ

ታወርዳቸዋለህ፤

ደም የተጠሙ ሰዎችና አታላዮች፣

የዘመናቸውን እኩሌታ አይኖሩም።

እኔ ግን በአንተ እታመናለሁ።

Священное Писание

Забур 55:1-14

Песнь 55

1Дирижёру хора. На мотив «О голубке в дальней дубраве». Мольба Давуда, когда филистимляне схватили его в Гате55:1 См. 1 Цар. 21:10-15; 27:1-4..

2Всевышний, помилуй меня,

потому что люди меня затравили;

всякий день, нападая, меня теснят.

3Враг травит меня всякий день;

как же много воюющих со мной,

о Высочайший!55:3 Или: «тех, кто в гордыне со мной воюет».

4Когда мне страшно,

я на Тебя полагаюсь.

5На Всевышнего, Чьё слово я славлю,

на Всевышнего полагаюсь

и не устрашусь:

что может мне сделать смертный?

6А мои враги всякий день искажают слова мои,

всегда замышляют сделать мне зло.

7Они составляют заговоры, таятся,

наблюдают за каждым моим шагом,

желая меня убить.

8Так не дай им избежать наказания за их вину;

в гневе Своём, Всевышний, низложи народы!

9У Тебя записаны все скитания мои;

собери мои слёзы в сосуд Свой –

не в Твоей ли книге они?

10И враги мои обратятся вспять,

когда я о помощи воззову.

Так я узнаю, что Всевышний со мной.

11На Всевышнего, Чьё слово я славлю,

на Вечного, Чьё слово я славлю,

12на Всевышнего полагаюсь

и не устрашусь:

что может мне сделать человек?

13Всевышний, я дам Тебе, что обещал;

я принесу Тебе жертвы благодарения.

14Ведь Ты спас меня от смерти

и не дал споткнуться моим ногам,

чтобы мне во свете живых

ходить пред Тобою.