መዝሙር 54 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 54:1-7

መዝሙር 54

ለፍትሕ አምላክ የቀረበ አቤቱታ

ለመዘምራን አለቃ፤ በበገናዎች፤ ዜፋውያን ወደ ሳኦል መጥተው፣ “ዳዊት በእኛ ዘንድ ተደብቋል” ባሉት ጊዜ፤ የዳዊት ትምህርት54 ርእሱ የሥነ ጽሑፉን ቅርጽ ወይም የመዝሙሩን ሁኔታ የሚያሳይ ሊሆን ይችላል።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ በስምህ አድነኝ፤

በኀይልህም ፍረድልኝ።

2እግዚአብሔር ሆይ፤ ጸሎቴን ስማልኝ፤

የአፌንም ቃል አድምጥ።

3ባዕዳን ተነሥተውብኛልና፤

ግፈኞች ነፍሴን ሽተዋታል፤

እግዚአብሔርንም ከምንም አልቈጠሩም። ሴላ

4እነሆ፤ እግዚአብሔር ረዳቴ ነው፤

ጌታም ደግፎ ይይዘኛል።

5የገዛ ክፋታቸው በሚያደቡብኝ ላይ ይመለስባቸው፤

በቃልህ ታማኝ ነህና አጥፋቸው።

6በበጎ ፈቃድ መሥዋዕት እሠዋልሃለሁ፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ መልካም ነውና፣

ለስምህ ምስጋና አቀርባለሁ፤

7ከመከራ ሁሉ ታድጎኛልና፤

ዐይኔም የጠላቶቼን ውድቀት ለማየት በቅቷል።

Ketab El Hayat

مزمور 54:1-7

الْمَزْمُورُ الرَّابِعُ وَالْخَمْسُونَ

لِقَائِدِ الْمُنْشِدِينَ عَلَى الآلاتِ الْوَتَرِيَّةِ. مَزْمُورٌ تَعْلِيمِيٌّ لِدَاوُدَ عِنْدَمَا قَالَ أَهْلُ زِيفَ لِشَاوُلَ إِنَّ دَاوُدَ مُخْتَبِئٌ عِنْدَهُمْ

1يَا اللهُ بِاسْمِكَ خَلِّصْنِي، وَبِقُوَّتِكَ أَنْصِفْنِي. 2يَا اللهُ اسْمَعْ صَلاتِي وَأَصْغِ إِلَى كَلامِي. 3لأَنَّ غُرَبَاءَ قَامُوا عَلَيَّ، وَعُتَاةً يَسْعَوْنَ إِلَى قَتْلِي، وَلَمْ يَجْعَلُوا اللهَ نُصْبَ أَعْيُنِهِمْ 4هُوَذَا اللهُ مُعِينِي وَالسَّيِّدُ الرَّبُّ عَاضِدِي. 5يَرُدُّ الشَّرَّ عَلَى أَعْدَائِي، وَبِحَقِّ (عَدْلِكَ) اسْتَأْصِلْهُمْ. 6طَوْعاً أَذْبَحُ لَكَ، وَأَحْمَدُ اسْمَكَ يَا رَبُّ لأَنَّهُ طَيِّبٌ. 7فَإِنَّهُ نَجَّانِي مِنْ كُلِّ ضيِقٍ وَرَأَيْتُ بِعْيَنيَّ (مَا حَلَّ) بِأَعْدَائِي.