መዝሙር 54 – NASV & KJV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 54:1-7

መዝሙር 54

ለፍትሕ አምላክ የቀረበ አቤቱታ

ለመዘምራን አለቃ፤ በበገናዎች፤ ዜፋውያን ወደ ሳኦል መጥተው፣ “ዳዊት በእኛ ዘንድ ተደብቋል” ባሉት ጊዜ፤ የዳዊት ትምህርት54 ርእሱ የሥነ ጽሑፉን ቅርጽ ወይም የመዝሙሩን ሁኔታ የሚያሳይ ሊሆን ይችላል።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ በስምህ አድነኝ፤

በኀይልህም ፍረድልኝ።

2እግዚአብሔር ሆይ፤ ጸሎቴን ስማልኝ፤

የአፌንም ቃል አድምጥ።

3ባዕዳን ተነሥተውብኛልና፤

ግፈኞች ነፍሴን ሽተዋታል፤

እግዚአብሔርንም ከምንም አልቈጠሩም። ሴላ

4እነሆ፤ እግዚአብሔር ረዳቴ ነው፤

ጌታም ደግፎ ይይዘኛል።

5የገዛ ክፋታቸው በሚያደቡብኝ ላይ ይመለስባቸው፤

በቃልህ ታማኝ ነህና አጥፋቸው።

6በበጎ ፈቃድ መሥዋዕት እሠዋልሃለሁ፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ መልካም ነውና፣

ለስምህ ምስጋና አቀርባለሁ፤

7ከመከራ ሁሉ ታድጎኛልና፤

ዐይኔም የጠላቶቼን ውድቀት ለማየት በቅቷል።

King James Version

Psalms 54:1-7

To the chief Musician on Neginoth, Maschil, A Psalm of David, when the Ziphims came and said to Saul, Doth not David hide himself with us?

1Save me, O God, by thy name, and judge me by thy strength.54.1 chief…: or, overseer54.1 Maschil: or, of instruction

2Hear my prayer, O God; give ear to the words of my mouth.

3For strangers are risen up against me, and oppressors seek after my soul: they have not set God before them. Selah.

4Behold, God is mine helper: the Lord is with them that uphold my soul.

5He shall reward evil unto mine enemies: cut them off in thy truth.54.5 mine…: Heb. those that observe me

6I will freely sacrifice unto thee: I will praise thy name, O LORD; for it is good.

7For he hath delivered me out of all trouble: and mine eye hath seen his desire upon mine enemies.