መዝሙር 52 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 52:1-9

መዝሙር 52

የክፉዎች ዕጣ ፈንታ

ለመዘምራን አለቃ፤ ኤዶማዊው ዶይቅ ወደ ሳኦል መጥቶ፣ “ዳዊት ወደ አቢሜሌክ ቤት መጥቷል” ብሎ በነገረው ጊዜ፤ የዳዊት52 ርእሱ ምናልባት የመዝሙሩን ሁኔታ የሚያሳይ ሊሆን ይችላል። ትምህርት።

1ኀያል ሆይ፤ በክፋት ለምን ትኵራራለህ?

አንተ በእግዚአብሔር ዐይን የተናቅህ፣

እንዴትስ ዘወትር ትታበያለህ?

2አንተ ማታለልን ሥራዬ ብለህ የያዝህ፤

አንደበትህ እንደ ሰላ ምላጭ፣

ጥፋትን ያውጠነጥናል።

3ከበጎ ነገር ይልቅ ክፋትን፣

እውነትን ከመናገር ይልቅ ሐሰትን ወደድህ። ሴላ

4አንተ አታላይ አንደበት ሆይ፤

ጐጂ ቃላትን ሁሉ ወደድህ!

5እግዚአብሔር ግን ለዘላለም

ያንኰታኵትሃል፤

ይነጥቅሃል፤ ከድንኳንህም መንጥቆ ያወጣሃል፤

ከሕያዋንም ምድር ይነቅልሃል። ሴላ

6ጻድቃን ይህን አይተው ይፈራሉ፤

እንዲህ እያሉም ይሥቁበታል፤

7“እግዚአብሔርን መጠጊያ ያላደረገ፣

ነገር ግን በሀብቱ ብዛት የተመካ፣

በክፋቱም የበረታ፣

ያ ሰው እነሆ!”

8እኔ ግን በእግዚአብሔር ቤት፣

እንደ ለመለመ የወይራ ዛፍ ነኝ፤

ከዘላለም እስከ ዘላለም፣

በእግዚአብሔር ምሕረት እታመናለሁ።

9ስላደረግኸው ነገር ለዘላለም አመሰግንሃለሁ፤

ስምህ መልካም ነውና፣ ስምህን ተስፋ አደርጋለሁ፤

በቅዱሳንም መካከል አመሰግንሃለሁ።

Thai New Contemporary Bible

สดุดี 52:1-9

สดุดี 52

(ถึงหัวหน้านักร้อง มัสคิล52:0 หัวเรื่องสดุดี 52 คงจะเป็นศัพท์ทางวรรณกรรมหรือทางดนตรีของดาวิด เมื่อโดเอกชาวเอโดมมาทูลซาอูลว่า “ดาวิดมาที่บ้านของอาหิเมเลค”)

1เจ้าคนเก่งกล้าเอ๋ย ทำไมจึงโอ้อวดในการชั่ว?

ทำไมยังคงยโสโอหังอยู่ทุกวี่วัน?

เจ้าผู้เป็นตัวอัปยศในสายพระเนตรของพระเจ้า

2ลิ้นของเจ้าวางแผนทำลายล้าง

ดั่งมีดโกนคมกริบ

เจ้าตวัดลิ้นตลบตะแลง

3เจ้ารักความชั่วมากกว่าความดี

และรักความเท็จยิ่งกว่าการพูดความจริง

เสลาห์

4เจ้ารักคำพูดให้ร้ายทุกคำ

เจ้าคนร้อยลิ้นกะลาวน!

5แน่ทีเดียว พระเจ้าจะนำเจ้าสู่ความพินาศนิรันดร์

พระองค์จะทรงกระชากเจ้าออกจากเต็นท์ของเจ้า

พระองค์จะทรงถอนรากถอนโคนเจ้าจากแดนผู้มีชีวิต

เสลาห์

6คนชอบธรรมจะเห็นและเกรงกลัว

จะหัวเราะเยาะเขาและพูดว่า

7“นี่แหละนะ คนที่ไม่ได้ยึดพระเจ้าเป็นที่มั่น

แต่พึ่งพาทรัพย์สมบัติมากมายของตน

และเรืองอำนาจขึ้นมาโดยการทำลายล้างผู้อื่น!”

8แต่ส่วนข้าพเจ้าเป็นเหมือนต้นมะกอก

งอกงามในพระนิเวศของพระเจ้า

ข้าพเจ้าพึ่งในความรักมั่นคงของพระเจ้า

ตลอดนิรันดร์

9ข้าพระองค์จะสรรเสริญพระองค์เป็นนิตย์ สำหรับสิ่งที่พระองค์ได้ทรงกระทำ

ข้าพระองค์จะฝากความหวังไว้กับพระนามของพระองค์เพราะพระนามนั้นประเสริฐ

ข้าพระองค์จะสรรเสริญพระองค์ต่อหน้าบรรดาประชากรของพระองค์