መዝሙር 52 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 52:1-9

መዝሙር 52

የክፉዎች ዕጣ ፈንታ

ለመዘምራን አለቃ፤ ኤዶማዊው ዶይቅ ወደ ሳኦል መጥቶ፣ “ዳዊት ወደ አቢሜሌክ ቤት መጥቷል” ብሎ በነገረው ጊዜ፤ የዳዊት52 ርእሱ ምናልባት የመዝሙሩን ሁኔታ የሚያሳይ ሊሆን ይችላል። ትምህርት።

1ኀያል ሆይ፤ በክፋት ለምን ትኵራራለህ?

አንተ በእግዚአብሔር ዐይን የተናቅህ፣

እንዴትስ ዘወትር ትታበያለህ?

2አንተ ማታለልን ሥራዬ ብለህ የያዝህ፤

አንደበትህ እንደ ሰላ ምላጭ፣

ጥፋትን ያውጠነጥናል።

3ከበጎ ነገር ይልቅ ክፋትን፣

እውነትን ከመናገር ይልቅ ሐሰትን ወደድህ። ሴላ

4አንተ አታላይ አንደበት ሆይ፤

ጐጂ ቃላትን ሁሉ ወደድህ!

5እግዚአብሔር ግን ለዘላለም

ያንኰታኵትሃል፤

ይነጥቅሃል፤ ከድንኳንህም መንጥቆ ያወጣሃል፤

ከሕያዋንም ምድር ይነቅልሃል። ሴላ

6ጻድቃን ይህን አይተው ይፈራሉ፤

እንዲህ እያሉም ይሥቁበታል፤

7“እግዚአብሔርን መጠጊያ ያላደረገ፣

ነገር ግን በሀብቱ ብዛት የተመካ፣

በክፋቱም የበረታ፣

ያ ሰው እነሆ!”

8እኔ ግን በእግዚአብሔር ቤት፣

እንደ ለመለመ የወይራ ዛፍ ነኝ፤

ከዘላለም እስከ ዘላለም፣

በእግዚአብሔር ምሕረት እታመናለሁ።

9ስላደረግኸው ነገር ለዘላለም አመሰግንሃለሁ፤

ስምህ መልካም ነውና፣ ስምህን ተስፋ አደርጋለሁ፤

በቅዱሳንም መካከል አመሰግንሃለሁ።

Japanese Contemporary Bible

詩篇 52:1-9

52

ダビデが、その敵ドエグ(Ⅰサムエル22章参照)に抗議して書いたもの。ドエグは、のちに八十五人の祭司とその家族を虐殺した。

1おまえは英雄のつもりでいるのか。

神の民に加えたこの暴虐を誇っているのか。

2おまえは策略を謀ることにかけては天才だ。

3どうしてそれほど、善より悪が、

真実よりうそが好きなのか。

4相手を中傷するのに目がなく、

でたらめを並べ立てては、平気で人を傷つける者よ。

5神はおまえを激しく打ち倒し、

死人の国へ引きずって行かれる。

6それを見て、神に従う人々は恐れを感じるが、

まもなく笑ってこう言うだろう。

7「あれが、神をあなどり、富に望みを置き、

ますます大胆に悪事を働いた者の末路だ。」

8一方、この私は、主に守られている

囲いの中のオリーブのようで、

いつまでも主のあわれみにすがる。

9ああ主よ。

あなたの懲らしめがどんなものかを知った私は、

永久にあなたをほめたたえて、

そのあわれみを待ち望みます。

あなたがどんなにいつくしみ深い神であるか、

知らない者などいないのですから。