መዝሙር 51 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 51:1-19

መዝሙር 51

የኀጢአት ኑዛዜ

ለመዘምራን አለቃ፤ ዳዊት ወደ ቤርሳቤህ ከገባ በኋላ፣ ነቢዩ ናታን ወደ እርሱ በመጣ ጊዜ፤ የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ እንደ ቸርነትህ መጠን፣

ምሕረት አድርግልኝ፤

እንደ ርኅራኄህም ብዛት፣

መተላለፌን ደምስስ።

2በደሌን ፈጽሞ ዕጠብልኝ፤

ከኀጢአቴም አንጻኝ።

3እኔ መተላለፌን ዐውቃለሁና፤

ኀጢአቴም ዘወትር በፊቴ ነው።

4በውሳኔህ ትክክል፣

በምትሰጠው ፍርድም ንጹሕ ትሆን ዘንድ፣

አንተን፣ በርግጥ አንተን ብቻ በደልሁ፤

በፊትህም ክፉ ነገር አደረግሁ።

5ስወለድ ጀምሮ በደለኛ፣

ገና እናቴም ስትፀንሰኝ ኀጢአተኛ ነኝ።

6እነሆ፤ እውነትን ከሰው ልብ ትሻለህ፤51፥6 በዕብራይስጡ የዚህ ሐረግ ትርጕም በትክክል አይታወቅም።

ስለዚህ ጥልቅ ጥበብን በውስጤ አስተምረኝ።51፥6 አስተምረህኛል ወይም ትፈልጋለህ ተብሎ መተርጐም ይቻላል።

7በሂሶጵ እርጨኝ፤ እኔም እነጻለሁ፤

ዕጠበኝ፤ ከበረዶም ይልቅ ነጭ እሆናለሁ።

8ሐሤትንና ደስታን አሰማኝ፤

ያደቀቅሃቸው ዐጥንቶቼም ደስ ይበላቸው።

9ፊትህን ከኀጢአቴ መልስ፤

በደሌንም ሁሉ ደምስስልኝ።

10አምላኬ ሆይ፤ ንጹሕ ልብ ፍጠርልኝ፤

ቀና የሆነውንም መንፈስ በውስጤ አድስ።

11ከፊትህ አትጣለኝ፤

ቅዱስ መንፈስህንም ከእኔ ላይ አትውሰድ።

12የማዳንህን ደስታ መልስልኝ፤

በእሽታ መንፈስም ደግፈህ ያዘኝ።

13እኔም ለሕግ ተላላፊዎች መንገድህን አስተምራለሁ፤

ኀጢአተኞችም ወደ አንተ ይመለሳሉ።

14የድነቴ አምላክ እግዚአብሔር ሆይ፤

ደም ከማፍሰስ አድነኝ፤

አንደበቴም ስለ ጽድቅህ በእልልታ ይዘምራል።

15ጌታ ሆይ ከንፈሮቼን ክፈት፤

አፌም ምስጋናህን ያውጃል።

16መሥዋዕትን ብትወድድ ኖሮ ባቀረብሁልህ ነበር፤

የሚቃጠል መሥዋዕትም ደስ አያሰኝህም።

17እግዚአብሔር የሚቀበለው መሥዋዕት የተሰበረ መንፈስ ነው፤51፥17 ወይም አምላክ ሆይ፤ የእኔ መሥዋዕት የተሰበረ

እግዚአብሔር ሆይ፤

አንተ የተሰበረውንና የተዋረደውን ልብ አትንቅም።

18በበጎ ፈቃድህ ጽዮንን አበልጽጋት፤

የኢየሩሳሌምንም ቅጥሮች ሥራ።

19የጽድቅ መሥዋዕት፣ የሚቃጠል መሥዋዕትና

ሙሉ የሚቃጠል መሥዋዕት ያን ጊዜ ደስ ያሰኙሃል፤

ኰርማዎች በመሠዊያህ ላይ የሚሠዉትም ያን ጊዜ ነው።

Japanese Contemporary Bible

詩篇 51:1-19

51

ダビデがバテ・シェバと姦通し、その夫ウリヤを殺したことに対し、預言者ナタンが神からの審判を告げた。その時のダビデの作。

1ああ、愛と恵みにあふれる神よ、私をあわれんで、

恐ろしい罪の汚れをぬぐい去ってください。

2どうか私を洗い、この罪からきよめて、

もう一度、潔白な身としてください。

3私は、自分がどんなに恥ずべきことをしたか、

よく存じております。

そのことで夜も昼も責めさいなまれているのです。

4私はあなたに、ただあなたに罪を犯し、

この恐ろしいことをしてしまいました。

すべてをご存じのあなたが下す判決に、

誤りはありません。

5私は生まれながらの罪人です。

母が私をみごもった時から、罪人でした。

6あなたがお喜びになるのは、

徹底した正直さです。

ああ、そのことを私に心底わからせてください。

7汚れをきよめる血を振り注いでください。

再び身も心もきれいになれるように、

私を洗ってください。

そうすれば、雪よりも白くなるでしょう。

8罰は受けます。

でもそののち、喜びを取り戻させてください。

9どうか、いつまでもこの罪を見続けず、

御目から消し去ってください。

10ああ神よ。

どうか、きよい思いと正しい願いで満たされた、

新しいきれいな心にしてください。

11私を見捨てて、永久に御前から

追放してしまわれることがありませんように。

聖霊を私から取り上げないでください。

12救いの喜びを再び鮮やかにして、

心からあなたに従おうとする思いに満たしてください。

13私のように罪深い人々に、

私はあなたの道を教えます。

きっと悔い改めて、あなたに立ち返ることでしょう。

14-15ああ神よ。

私の頼むところはあなただけですから、

どうか死刑の宣告を下さないでください。

助けてくださるなら、私の舌はゆるみ、

あなたの赦しを高らかに歌いだすでしょう。

ああ、私はどれほどあなたをほめたたえることでしょう。

16あなたは罪滅ぼしに何かをせよとはおっしゃいません。

もしそう言われるなら、

喜んで仰せに従うことでしょう。

あなたは、祭壇で焼かれる供え物を

求めておられるわけではありません。

17あなたがお望みなのは、悔い改めて、

くずおれたたましいです。

ああ神よ。

罪を深く後悔して砕かれた心にこそ、

あなたは目を留めてくださるのです。

18どうか主よ、私の罪のために

イスラエルの国を罰しないでください。

あなたの民を助け、エルサレムをお守りください。

19私が潔白の身となってはじめて、

あなたは私の善行と、祭壇に供えるいけにえの雄牛とを、

喜んで受け入れてくださることでしょう。