መዝሙር 5 – NASV & NIV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 5:1-12

መዝሙር 5

የጧት ጸሎት

ለመዘምራን አለቃ፤ በዋሽንት የሚዘመር፣ የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ ቃሌን አድምጥ፤

መቃተቴንም ቸል አትበል።

2ንጉሤና አምላኬ ሆይ፤

ወደ አንተ እጸልያለሁና፣

ድረስልኝ ብዬ ስጮኽ ስማኝ።

3እግዚአብሔር ሆይ፤ በማለዳ ድምፄን ትሰማለህ፤

በማለዳ ልመናዬን በፊትህ አቀርባለሁ፤

ፈቃድህንም በጥሞና እጠባበቃለሁ፤

4አንተ በክፋት ደስ የምትሰኝ አምላክ አይደለህም፤

ክፉም ከአንተ ጋር አያድርም።

5እብሪተኞች በፊትህ መቆም አይችሉም፤

ክፉ አድራጊዎችንም ሁሉ ጠላህ።

6ሐሰት የሚናገሩትን ታጠፋቸዋለህ፤

ደም የተጠሙትንና አታላዮችን፣

እግዚአብሔር ይጸየፋቸዋል።

7እኔ ግን በምሕረትህ ብዛት

ወደ ቤትህ እገባለሁ፤

አንተንም በመፍራት፣

ወደ ተቀደሰው መቅደስህ እሰግዳለሁ።

8እግዚአብሔር ሆይ፤ ከጠላቶቼ የተነሣ፣

በጽድቅህ ምራኝ፤

መንገድህንም በፊቴ አቅናልኝ።

9በንግግራቸው ውስጥ እውነት የለም፤

ልባቸው የጥፋት ጐሬ ነው፤

ጕረሯቸው የተከፈተ መቃብር ነው፤

በምላሳቸውም ይሸነግላሉ።

10አምላክ ሆይ፤ የእጃቸውን ስጣቸው!

ተንኰላቸው መውደቂያቸው ይሁን፤

ከኀጢአታቸው ብዛት የተነሣ አስወግዳቸው፣

በአንተ ላይ ዐምፀዋልና።

11አንተን መጠጊያ የሚያደርጉ ሁሉ ግን ደስ ይበላቸው፤

ዘላለም በደስታ ይዘምሩ፤

ስምህን የሚወድዱ በአንተ ደስ እንዲላቸው፣

ተከላካይ ሁንላቸው።

12እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ጻድቃንን ትባርካቸዋለህ፤

በሞገስህም እንደ ጋሻ ትከልላቸዋለህ።

New International Version

Psalms 5:1-12

Psalm 5In Hebrew texts 5:1-12 is numbered 5:2-13.

For the director of music. For pipes. A psalm of David.

1Listen to my words, Lord,

consider my lament.

2Hear my cry for help,

my King and my God,

for to you I pray.

3In the morning, Lord, you hear my voice;

in the morning I lay my requests before you

and wait expectantly.

4For you are not a God who is pleased with wickedness;

with you, evil people are not welcome.

5The arrogant cannot stand

in your presence.

You hate all who do wrong;

6you destroy those who tell lies.

The bloodthirsty and deceitful

you, Lord, detest.

7But I, by your great love,

can come into your house;

in reverence I bow down

toward your holy temple.

8Lead me, Lord, in your righteousness

because of my enemies—

make your way straight before me.

9Not a word from their mouth can be trusted;

their heart is filled with malice.

Their throat is an open grave;

with their tongues they tell lies.

10Declare them guilty, O God!

Let their intrigues be their downfall.

Banish them for their many sins,

for they have rebelled against you.

11But let all who take refuge in you be glad;

let them ever sing for joy.

Spread your protection over them,

that those who love your name may rejoice in you.

12Surely, Lord, you bless the righteous;

you surround them with your favor as with a shield.