መዝሙር 49 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 49:1-20

መዝሙር 49

የሀብት ከንቱነት

ለመዘምራን አለቃ፤ የቆሬ ልጆች መዝሙር።

1እናንተ ሕዝቦች ሁላችሁ፤ ይህን ስሙ፤

በዓለም የምትኖሩ ሁሉ፤ ይህን አድምጡ።

2ዝቅተኞችና ከፍተኞች፤

ባለጠጎችና ድኾች ይህን በአንድነት ስሙ።

3አፌ የጥበብን ቃል ይናገራል፤

የልቤም ሐሳብ ማስተዋልን ይሰጣል።

4ጆሮዬን ወደ ምሳሌ አዘነብላለሁ፤

እንቆቅልሼንም በበገና እፈታለሁ።

5የአጭበርባሪዎች ክፋት በከበበኝ ጊዜ፣

በክፉ ቀን ለምን እፈራለሁ?

6በሀብታቸው የሚመኩትን፣

በብልጽግናቸውም የሚታመኑትን ለምን እፈራለሁ?

7የሌላውን ሕይወት መቤዠት የሚችል ሰው፣

ወይም ለእግዚአብሔር ወጆ የሚከፍልለት ማንም የለም።

8የነፍስ ቤዛ ውድ ነውና፤

በቂ ዋጋም ከቶ ሊገኝለት አይችልም፤

9በዚህም ዘላለም ይኖራል፣

መበስበስንም አያይም።

10ጠቢባን ሟቾች መሆናቸው የሚታይ ነው፤

ቂልና ሞኝም በአንድነት ይጠፋሉ፤

ጥሪታቸውንም ለሌላው ጥለው ይሄዳሉ።

11መሬቶችን በስማቸው ቢሰይሙም፣

መቃብራቸው የዘላለም ቤታቸው፣

ከትውልድ እስከ ትውልድም መኖሪያቸው ይሆናል።

12ሰው በሀብቱ እንደ ተከበረ አይዘልቅም፤

ታይተው የሚጠፉ እንስሳትን ይመስላል።49፥12 በሰብዓ ሊቃናት ትርጕምና በሱርስቱ ቅጅ 12 ከ20 ጋር አንድ ዐይነት ነው፤ ዕብራይስጡ ግን ከዚህ ይለያል።

13ይህ የተላላዎች ዕድል ፈንታ፣

የእነርሱንም አባባል ተቀብለው ለሚከተሏቸው፣

መጨረሻ ግብ ነው። ሴላ

14እንደ በጎች ለሲኦል49፥14 በዚህ እና በ15 ላይ ዕብራይስጡ ከዚህ ጋር ይስማማል፤ አንዳንድ የእንግሊዝኛ ቅጆች ግን መቃብር ይላሉ። የተዳረጉ ናቸው፤

ሞትም እረኛቸው ይሆናል፤

ቅኖች በማለዳ ይገዟቸዋል፤

አካላቸው ከክብር ቤታቸው ርቆ፣

በሲኦል ይፈራርሳል።

15እግዚአብሔር ግን ነፍሴን49፥15 ወይም ሕይወቴን ከሲኦል እጅ ይቤዣታል፤

በርግጥም በእርሱ ዘንድ ተቀባይነት አለኝ። ሴላ

16ሰው ባለጠጋ ሲሆን፣

የቤቱም ክብር ሲበዛለት አትፍራ፤

17በሚሞትበትም ጊዜ ይዞት የሚሄደው አንዳች የለምና፤

ክብሩም አብሮት አይወርድም።

18በሕይወት ሳለ ራሱን እንደ ተባረከ ቢቈጥርም፣

ሰዎች በበለጸግህ ጊዜ ቢያወድሱህም፣

19ብርሃን ከቶ ወደማያዩት፣

ወደ አባቶች ማኅበር ይቀላቀላል።

20ሰው በሀብቱ እንደ ተከበረ አይዘልቅም፤

ታይተው የሚጠፉ እንስሳትን ይመስላል።

Thai New Contemporary Bible

สดุดี 49:1-20

สดุดี 49

(ถึงหัวหน้านักร้อง บทสดุดีของบุตรโคราห์)

1ชนชาติทั้งปวงเอ๋ย จงฟังทางนี้

ทุกคนทั่วโลกจงฟัง

2ทั้งผู้ใหญ่และผู้น้อย

คนจนและคนรวย

3ปากของข้าพเจ้าจะกล่าวถ้อยคำแห่งสติปัญญา

เนื้อความจากใจของข้าพเจ้านี้จะให้ความเข้าใจ

4ข้าพเจ้าจะเอียงหูฟังภาษิต

ข้าพเจ้าจะใช้พิณขานไขปริศนา

5ทำไมข้าพเจ้าต้องกลัวยามตกที่นั่งลำบาก

เมื่อคนเจ้าเล่ห์ชั่วร้ายรุมล้อมข้าพเจ้า?

6คนพวกนั้นพึ่งพิงทรัพย์สมบัติ

และอวดอ้างความร่ำรวยเหลือล้นของตน

7ไม่มีสักคนไถ่ชีวิตให้ใครได้

หรือถวายค่าไถ่ชีวิตของเขาแด่พระเจ้า

8ค่าไถ่สำหรับชีวิตหนึ่งนั้นแพงนัก

ชดใช้แค่ไหนก็ไม่พอ

9เพื่อให้เขามีชีวิตอยู่ชั่วนิรันดร์

และไม่ต้องพบกับความเน่าเปื่อย

10เพราะทุกคนก็เห็นว่าคนมีปัญญาก็ตาย

คนโง่และคนสิ้นคิดก็ย่อยยับเหมือนกัน

และเขาทิ้งทรัพย์สมบัติของตนไว้ให้คนอื่น

11หลุมศพของเขาจะเป็นบ้านของเขา49:11 ภาษาฮีบรูว่าในความคิดของพวกเขา บ้านของพวกเขาจะคงอยู่ ตลอดกาล

เป็นที่อาศัยตลอดทุกชั่วอายุ

แม้พวกเขาได้ตั้งชื่อ49:11 หรือเพราะพวกเขาได้ตั้งชื่อดินแดนตามชื่อของตัว

12แต่มนุษย์ไม่ว่าจะร่ำรวยสักปานใดก็ไม่อาจมีชีวิตอยู่ได้ตลอดไป

เขา49:12 ฉบับ LXX. และ Syr. ข้อ 12 เหมือนกับข้อ 20เหมือนสัตว์เดียรัจฉานที่ต้องจบชีวิตลง

13นี่แหละคือชะตากรรมของคนที่วางใจตัวเอง

และของสาวกที่เห็นชอบกับคำสอนของเขา

เสลาห์

14เขาเป็นเหมือนแกะที่ถูกกำหนดไว้สำหรับหลุมฝังศพ

และความตายจะมากัดกินเขา

ผู้เที่ยงธรรมจะปกครองเหนือพวกเขาในยามรุ่งอรุณ

ร่างของเขาจะเน่าเปื่อยในหลุมศพ

ห่างไกลจากคฤหาสน์อันโอ่อ่าของตน

15แต่พระเจ้าจะทรงไถ่ชีวิต49:15 หรือวิญญาณของข้าพเจ้าให้พ้นจากอำนาจของหลุมฝังศพ

พระองค์จะทรงรับข้าพเจ้าไว้แน่นอน

เสลาห์

16ไม่ต้องหวั่นวิตกเมื่อใครคนหนึ่งร่ำรวยขึ้น

เมื่อบ้านของเขาโอ่อ่าตระการขึ้น

17เพราะเมื่อเขาตาย เขาเอาอะไรไปด้วยไม่ได้

ความเลิศหรูของเขาจะไม่ตามเขาลงไป

18แม้ขณะมีชีวิตอยู่เขาเรียกตัวเองว่าผู้เป็นสุข

และผู้คนยกย่องในยามที่เขารุ่งโรจน์

19เขาจะไปอยู่กับบรรพบุรุษของเขา

ผู้ซึ่งไม่เคยเห็นแสงแห่งชีวิต

20ผู้ที่มีทรัพย์สมบัติแต่ปราศจากความเข้าใจ

ก็เหมือนสัตว์เดียรัจฉานที่ต้องจบชีวิตลง