መዝሙር 49 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 49:1-20

መዝሙር 49

የሀብት ከንቱነት

ለመዘምራን አለቃ፤ የቆሬ ልጆች መዝሙር።

1እናንተ ሕዝቦች ሁላችሁ፤ ይህን ስሙ፤

በዓለም የምትኖሩ ሁሉ፤ ይህን አድምጡ።

2ዝቅተኞችና ከፍተኞች፤

ባለጠጎችና ድኾች ይህን በአንድነት ስሙ።

3አፌ የጥበብን ቃል ይናገራል፤

የልቤም ሐሳብ ማስተዋልን ይሰጣል።

4ጆሮዬን ወደ ምሳሌ አዘነብላለሁ፤

እንቆቅልሼንም በበገና እፈታለሁ።

5የአጭበርባሪዎች ክፋት በከበበኝ ጊዜ፣

በክፉ ቀን ለምን እፈራለሁ?

6በሀብታቸው የሚመኩትን፣

በብልጽግናቸውም የሚታመኑትን ለምን እፈራለሁ?

7የሌላውን ሕይወት መቤዠት የሚችል ሰው፣

ወይም ለእግዚአብሔር ወጆ የሚከፍልለት ማንም የለም።

8የነፍስ ቤዛ ውድ ነውና፤

በቂ ዋጋም ከቶ ሊገኝለት አይችልም፤

9በዚህም ዘላለም ይኖራል፣

መበስበስንም አያይም።

10ጠቢባን ሟቾች መሆናቸው የሚታይ ነው፤

ቂልና ሞኝም በአንድነት ይጠፋሉ፤

ጥሪታቸውንም ለሌላው ጥለው ይሄዳሉ።

11መሬቶችን በስማቸው ቢሰይሙም፣

መቃብራቸው የዘላለም ቤታቸው፣

ከትውልድ እስከ ትውልድም መኖሪያቸው ይሆናል።

12ሰው በሀብቱ እንደ ተከበረ አይዘልቅም፤

ታይተው የሚጠፉ እንስሳትን ይመስላል።49፥12 በሰብዓ ሊቃናት ትርጕምና በሱርስቱ ቅጅ 12 ከ20 ጋር አንድ ዐይነት ነው፤ ዕብራይስጡ ግን ከዚህ ይለያል።

13ይህ የተላላዎች ዕድል ፈንታ፣

የእነርሱንም አባባል ተቀብለው ለሚከተሏቸው፣

መጨረሻ ግብ ነው። ሴላ

14እንደ በጎች ለሲኦል49፥14 በዚህ እና በ15 ላይ ዕብራይስጡ ከዚህ ጋር ይስማማል፤ አንዳንድ የእንግሊዝኛ ቅጆች ግን መቃብር ይላሉ። የተዳረጉ ናቸው፤

ሞትም እረኛቸው ይሆናል፤

ቅኖች በማለዳ ይገዟቸዋል፤

አካላቸው ከክብር ቤታቸው ርቆ፣

በሲኦል ይፈራርሳል።

15እግዚአብሔር ግን ነፍሴን49፥15 ወይም ሕይወቴን ከሲኦል እጅ ይቤዣታል፤

በርግጥም በእርሱ ዘንድ ተቀባይነት አለኝ። ሴላ

16ሰው ባለጠጋ ሲሆን፣

የቤቱም ክብር ሲበዛለት አትፍራ፤

17በሚሞትበትም ጊዜ ይዞት የሚሄደው አንዳች የለምና፤

ክብሩም አብሮት አይወርድም።

18በሕይወት ሳለ ራሱን እንደ ተባረከ ቢቈጥርም፣

ሰዎች በበለጸግህ ጊዜ ቢያወድሱህም፣

19ብርሃን ከቶ ወደማያዩት፣

ወደ አባቶች ማኅበር ይቀላቀላል።

20ሰው በሀብቱ እንደ ተከበረ አይዘልቅም፤

ታይተው የሚጠፉ እንስሳትን ይመስላል።

Ketab El Hayat

مزمور 49:1-20

الْمَزْمُورُ التَّاسِعُ وَالأَرْبَعُونَ

لِقَائِدِ الْمُنْشِدِينَ. مَزْمُورٌ لِبَنِي قُورَحَ

1اسْمَعُوا هَذَا يَا جَمِيعَ الشُّعُوبِ، أَصْغُوا يَا جَمِيعَ سُكَّانِ الْعَالَمِ. 2(اسْمَعُوا) إِلَيَّ أَيُّهَا الْعُظَمَاءُ، الأَغْنِيَاءُ وَالْفُقَرَاءُ عَلَى السَّوَاءِ. 3يَنْطِقُ فَمِي بِالْحِكْمَةِ، وَخَوَاطِرُ قَلْبِي بِالْفَهْمِ. 4أُعِيرُ أُذُنِي لأَسْمَعَ مَثَلاً، وَعَلَى عَزْفِ الْعُودِ أَشْرَحُ لُغْزِي.

5لِمَاذَا أَخَافُ فِي أَيَّامِ الْخَطَرِ عِنْدَمَا يُحِيطُ بِي شَرُّ مُطَارِدِيَّ؟ 6أُولَئِكَ الْمُتَّكِلُونَ عَلَى ثَرْوَتِهِمْ، وَبِوَفْرَةِ غِنَاهُمْ يَفْتَخِرُونَ. 7لَا يَقْدِرُ أَحَدٌ أَبَداً أَنْ يَفْتَدِيَ أَخَاهُ أَوْ يُقَدِّمَ لِلهِ كَفَّارَةً عَنْهُ. 8لأَنَّ فِدْيَةَ النُّفُوسِ بَاهِظَةٌ يَتَعَذَّرُ دَفْعُهَا مَدَى الْحَيَاةِ 9طَلَباً لِلْخُلُودِ عَلَى الأَرْضِ وَتَفَادِياً لِرُؤْيَةِ الْقَبْرِ. 10لَكِنَّ الْحُكَمَاءَ يَمُوتُونَ كَمَا يَمُوتُ الْجَاهِلُ وَالْغَبِيُّ، تَارِكِينَ ثَرْوَتَهُمْ لِغَيْرِهِمْ. 11يَتَوَهَّمُونَ أَنَّ بُيُوتَهُمْ خَالِدَةٌ، وَأَنَّ مَسَاكِنَهُمْ بَاقِيَةٌ مِنْ جِيلٍ إِلَى جِيلٍ، فَأَطْلَقُوا أَسْمَاءَهُمْ عَلَى أَرَاضِيهِمْ (تَخْلِيداً لِذِكْرِهِمْ). 12وَلَكِنَّ الإِنْسَانَ لَا يَخْلُدُ فِي أُبَّهَتِهِ. إِنَّهُ يُمَاثِلُ الْبَهَائِمَ الَّتِي تُبَادُ. 13هَذَا هُوَ مَصِيرُ الْجُهَّالِ الْوَاثِقِينَ بِأَنْفُسِهِمْ، وَمَصِيرُ أَعْقَابِهِمِ الَّذِينَ يَسْتَحْسِنُونَ أَقْوَالَهُمْ. 14يُسَاقُونَ لِلْمَوْتِ كَالأَغْنَامِ، وَيَكُونُ الْمَوْتُ رَاعِيَهُمْ وَيَسُودُ الْمُسْتَقِيمُونَ عَلَيْهِمْ. تَبْلَى صُورَتُهُمْ، وَتَصِيرُ الْهَاوِيَةُ مَسْكَنَهُمْ. 15إِنَّمَا اللهُ يَفْتَدِي نَفْسِي مِنْ قَبْضَةِ الْهَاوِيَةِ إذْ يَأْخُذُنِي إِلَيْهِ.

16لَا تَخْشَ إِذَا اغْتَنَى إِنْسَانٌ، وَزَادَ مَجْدُ بَيْتِهِ. 17فَإِنَّهُ عِنْدَ مَوْتِهِ لَا يَأْخُذُ مَعَهُ شَيْئاً، وَلَا يَلْحَقُ بِهِ مَجْدُهُ إِلَى قَبْرِهِ. 18وَمَعَ أَنَّهُ يُنَعِّمُ نَفْسَهُ بِالْبَرَكَاتِ فِي أَثْنَاءِ حَيَاتِهِ وَيُطْرِيهِ النَّاسُ إذْ أَحْسَنَ إِلَى نَفْسِهِ، 19إلّا أَنَّ نَفْسَهُ سَتَلْحَقُ بِآبَائِهِ، الَّذِينَ لَا يَرَوْنَ النُّورَ إِلَى الأَبَدِ. 20فَالإِنْسَانُ الْمُتَمَتِّعُ بِالْكَرَامَةِ مِنْ غَيْرِ فَهْمٍ، يُمَاثِلُ الْبَهَائِمَ البَائِدَةَ.