መዝሙር 48 – NASV & CST

New Amharic Standard Version

መዝሙር 48:1-14

መዝሙር 48

የእግዚአብሔር ተራራ ጽዮን

ዝማሬ፤ የቆሬ ልጆች መዝሙር።

1እግዚአብሔር ታላቅ ነው፤

በአምላካችን ከተማ በተቀደሰው ተራራ ከፍ ያለ ምስጋና ይገባዋል።

2የምድር ሁሉ ደስታ የሆነው፣

በሰሜን በኩል48፥2 ጻፎን የሚለው የዕብራይስጡ ቃል የተቀደሰ ተራራን ወይም የሰሜንን አቅጣጫ ሊያመለክት ይችላል። በርቀት የሚታየው፣

በከፍታ ላይ አምሮ የደመቀው የጽዮን ተራራ፣

የታላቁ ንጉሥ ከተማ ነው።

3እግዚአብሔር በአዳራሾቿ ውስጥ ሆኖ፤

ብርቱ ምሽግ እንደ ሆናት አስመስክሯል።

4እነሆ፤ ነገሥታት ተባብረው መጡ፤

አንድ ላይ ሆነውም ገሠገሡ።

5አይተውም ተደነቁ፤

ደንግጠውም ፈረጠጡ።

6ምጥ እንደ ያዛት ሴት፣

በዚያ ብርክ ያዛቸው።

7የምሥራቅ ነፋስ የተርሴስን መርከብ እንደሚሰባብር፣

አንተ አብረከረክሃቸው።

8እንደ ሰማን፣

በሰራዊት አምላክ ከተማ፣

በአምላካችን ከተማ፣

እንዲሁ አየን፤

እግዚአብሔር ለዘላለም ያጸናታል። ሴላ

9አምላክ ሆይ፤ በቤተ መቅደስህ ውስጥ ሆነን፣

ምሕረትህን እናስባለን።

10አምላክ ሆይ፤ ምስጋናህ እንደ ስምህ፣

እስከ ምድር ዳርቻ ይዘልቃል፤

ቀኝ እጅህም ጽድቅን የተሞላች ናት።

11ስለ ፍርድህ፣

የጽዮን ተራራ ሐሤት ታድርግ፤

የይሁዳ መንደሮችም ደስ ይበላቸው።

12በጽዮን አካባቢ ተመላለሱ፤ ዙሪያዋንም ሂዱ፤

የጥበቃ ግንቦቿንም ቍጠሩ፤

13ለሚቀጥለው ትውልድ ትናገሩ ዘንድ፣

መከላከያ ዕርዶቿን ልብ ብላችሁ ተመልከቱ፤

መጠበቂያ ማማዎቿን እዩ።

14ይህ አምላክ ከዘላለም እስከ ዘላለም አምላካችን ነውና፤

እስከ መጨረሻው የሚመራንም እርሱ ነው።

Nueva Versión Internacional (Castilian)

Salmo 48:1-14

Salmo 48

Canción. Salmo de los hijos de Coré.

1Grande es el Señor, y digno de suprema alabanza

en la ciudad de nuestro Dios.

Su monte santo, 2bella colina,

es la alegría de toda la tierra.

El monte Sión, en la parte norte,

es la ciudad del gran Rey.

3En las fortificaciones de Sión

Dios se ha dado a conocer como refugio seguro.

4Hubo reyes que unieron sus fuerzas

y que juntos avanzaron contra la ciudad;

5pero al verla quedaron pasmados,

y asustados emprendieron la retirada.

6Allí el miedo se apoderó de ellos,

y un dolor de parturienta les sobrevino.

7¡Con un viento huracanado

destruiste las naves de Tarsis!

8Tal como lo habíamos oído,

ahora lo hemos visto

en la ciudad del Señor Todopoderoso,

en la ciudad de nuestro Dios:

¡Él la hará permanecer para siempre! Selah

9Dentro de tu templo, oh Dios,

meditamos en tu gran amor.

10Tu alabanza, oh Dios, como tu nombre,

llega a los confines de la tierra;

tu derecha está llena de justicia.

11A causa de tus justas decisiones

el monte Sión se alegra

y las aldeas de Judá se regocijan.

12Caminad alrededor de Sión,

caminad en torno a él

y contad sus torres.

13Observad bien sus murallas

y examinad sus fortificaciones,

para que se lo cuenten a las generaciones futuras.

14¡Este Dios es nuestro Dios eterno!

¡Él nos guiará para siempre!48:14 para siempre (LXX); sobre muerte (TM).