መዝሙር 47 – NASV & PCB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 47:1-9

መዝሙር 47

እግዚአብሔር፣ የእስራኤል ንጉሥና የዓለም ጌታ

ለመዘምራን አለቃ፤ የቆሬ ልጆች መዝሙር።

1ሕዝቦች ሁላችሁ እጆቻችሁን አጨብጭቡ፤

ድምፃችሁን ከፍ አድርጋችሁ ለእግዚአብሔር እልል በሉ።

2በምድር ሁሉ ላይ ታላቅ የሆነው ንጉሥ፣

ልዑል እግዚአብሔር የሚያስፈራ ነውና።

3ሕዝቦችን ከእኛ በታች አደረገ፤

መንግሥታትንም ከእግራችን ሥር አስገዛልን።

4ለሚወድደው ለያዕቆብ ክብር የሆነችውን፣

ርስታችንን እርሱ መረጠልን። ሴላ

5አምላክ በእልልታ፣

እግዚአብሔር በመለከት ድምፅ ዐረገ።

6አምላካችንን አወድሱት፤ አወድሱት፤

ንጉሣችንን አወድሱት፤ አወድሱት፤

7እግዚአብሔር የምድር ሁሉ ንጉሥ ነውና፤

ምርጥ ዝማሬ47፥7 ዕብራይስጡ ማስኪል ይላል፤ ይኸውም የሥነ ጽሑፉን ቅርጽ ወይም የሙዚቃውን ሁኔታ የሚያሳይ ሊሆን ይችላል። አቅርቡለት።

8እግዚአብሔር በሕዝቦች ላይ ነግሧል፤

እግዚአብሔር በተቀደሰ ዙፋኑ ላይ ተቀምጧል።

9ከአብርሃም አምላክ ሕዝብ ጋር፣

የሕዝቦች መኳንንት ተሰበሰቡ፤

የምድር ነገሥታት47፥9 ወይም ጋሾች የእግዚአብሔር ናቸውና፤

እርሱም እጅግ ከፍ ከፍ ያለ ነው።

Persian Contemporary Bible

مزامير 47:1-9

پادشاه تمام جهان

1ای همهٔ مردم جهان، دست بزنيد و شادی كنيد! خدا را با سرودهای شاد پرستش كنيد! 2زيرا خداوند متعال و پرهيبت است. او پادشاهی است با عظمت كه بر سراسر جهان فرمان می‌راند. 3او قومها را مغلوب ما ساخت، طايفه‌ها را به زير پای ما انداخت 4و سرزمينی برای سكونت ما برگزيد، سرزمينی كه موجب افتخار قوم عزيز اوست.

5خداوند در ميان غريو شادی و صدای شيپور، به تخت خود صعود نموده است! 6در ستايش او سرود بخوانيد! پادشاه ما را با سرود پرستش كنيد! 7خدا پادشاه تمام جهان است؛ او را با سرود ستايش كنيد! 8خدا بر قومهای جهان فرمان می‌راند. او بر تخت مقدس خود نشسته است. 9رؤسای ممالک جهان با ما متحد شده‌اند تا با ما خدای ابراهيم را پرستش كنند، زيرا او قدرتمندتر از تمام جنگاوران و برتر از همه مردم جهان می‌باشد.