መዝሙር 47 – NASV & NIVUK

New Amharic Standard Version

መዝሙር 47:1-9

መዝሙር 47

እግዚአብሔር፣ የእስራኤል ንጉሥና የዓለም ጌታ

ለመዘምራን አለቃ፤ የቆሬ ልጆች መዝሙር።

1ሕዝቦች ሁላችሁ እጆቻችሁን አጨብጭቡ፤

ድምፃችሁን ከፍ አድርጋችሁ ለእግዚአብሔር እልል በሉ።

2በምድር ሁሉ ላይ ታላቅ የሆነው ንጉሥ፣

ልዑል እግዚአብሔር የሚያስፈራ ነውና።

3ሕዝቦችን ከእኛ በታች አደረገ፤

መንግሥታትንም ከእግራችን ሥር አስገዛልን።

4ለሚወድደው ለያዕቆብ ክብር የሆነችውን፣

ርስታችንን እርሱ መረጠልን። ሴላ

5አምላክ በእልልታ፣

እግዚአብሔር በመለከት ድምፅ ዐረገ።

6አምላካችንን አወድሱት፤ አወድሱት፤

ንጉሣችንን አወድሱት፤ አወድሱት፤

7እግዚአብሔር የምድር ሁሉ ንጉሥ ነውና፤

ምርጥ ዝማሬ47፥7 ዕብራይስጡ ማስኪል ይላል፤ ይኸውም የሥነ ጽሑፉን ቅርጽ ወይም የሙዚቃውን ሁኔታ የሚያሳይ ሊሆን ይችላል። አቅርቡለት።

8እግዚአብሔር በሕዝቦች ላይ ነግሧል፤

እግዚአብሔር በተቀደሰ ዙፋኑ ላይ ተቀምጧል።

9ከአብርሃም አምላክ ሕዝብ ጋር፣

የሕዝቦች መኳንንት ተሰበሰቡ፤

የምድር ነገሥታት47፥9 ወይም ጋሾች የእግዚአብሔር ናቸውና፤

እርሱም እጅግ ከፍ ከፍ ያለ ነው።

New International Version – UK

Psalms 47:1-9

Psalm 47In Hebrew texts 47:1-9 is numbered 47:2-10.

For the director of music. Of the Sons of Korah. A psalm.

1Clap your hands, all you nations;

shout to God with cries of joy.

2For the Lord Most High is awesome,

the great King over all the earth.

3He subdued nations under us,

peoples under our feet.

4He chose our inheritance for us,

the pride of Jacob, whom he loved.47:4 The Hebrew has Selah (a word of uncertain meaning) here.

5God has ascended amid shouts of joy,

the Lord amid the sounding of trumpets.

6Sing praises to God, sing praises;

sing praises to our King, sing praises.

7For God is the King of all the earth;

sing to him a psalm of praise.

8God reigns over the nations;

God is seated on his holy throne.

9The nobles of the nations assemble

as the people of the God of Abraham,

for the kings47:9 Or shields of the earth belong to God;

he is greatly exalted.