መዝሙር 46 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 46:1-11

መዝሙር 4646 ርእስ ምናልባት የሙዚቃውን ሁኔታ ሊያሳይ ይችላል።

እግዚአብሔር ከእኛ ጋር

ለመዘምራን አለቃ፤ የቆሬ ልጆች መዝሙር፤ በደናግል የዜማ ስልት የሚዘመር መዝሙር።

1አምላካችን መጠጊያችንና ኀይላችን፣

በሚደርስብን መከራ ሁሉ የቅርብ ረዳታችን ነው።

2ስለዚህ ምድር ብትነዋወጥ እንኳ፣

ተራሮችም ወደ ባሕር ጥልቅ ቢሰምጡ አንፈራም።

3ውሆች ቢያስገመግሙ፣ ዐረፋ ቢደፍቁም፣ ተራሮችም ከውሆቹ ሙላት የተነሣ

ቢንቀጠቀጡም አንደናገጥም። ሴላ

4የእግዚአብሔርን ከተማ፣

የልዑልን የተቀደሰ ማደሪያ ደስ የሚያሰኙ የወንዝ ፈሳሾች አሉ።

5እግዚአብሔር በመካከሏ ነው፤ አትናወጥም፤

አምላክ በማለዳ ይረዳታል።

6ሕዝቦች በዐመፅ ተነሡ፤ መንግሥታትም ወደቁ፤

ድምፁን ከፍ አድርጎ አሰማ፤ ምድርም ቀለጠች።

7የሰራዊት አምላክ ከእኛ ጋር ነው፤

የያዕቆብ አምላክ መጠጊያችን ነው። ሴላ

8ኑና የእግዚአብሔርን ሥራ፣

ምድርንም እንዴት ባድማ እንዳደረጋት እዩ።

9ከዳር እስከ ዳር ጦርነትን ከምድር ያስወግዳል፤

ቀስትን ይሰብራል፤ ጦርን ያነክታል፤

ጋሻንም46፥9 ወይም ሠረገላንም በእሳት ያቃጥላል።

10“ዕረፉ፤ እኔም አምላክ እንደ ሆንሁ ዕወቁ፤

በሕዝቦች ዘንድ ከፍ ከፍ እላለሁ፤

በምድርም ላይ ከፍ ከፍ እላለሁ።”

11የሰራዊት አምላክ ከእኛ ጋር ነው፤

የያዕቆብ አምላክ መጠጊያችን ነው። ሴላ

Thai New Contemporary Bible

สดุดี 46:1-11

สดุดี 46

(ถึงหัวหน้านักร้อง บทเพลงของบุตรโคราห์ ตามทำนองอาลาโมธ)

1พระเจ้าทรงเป็นที่ลี้ภัยและเป็นกำลังของเรา

เป็นความช่วยเหลือที่พร้อมเสมอในยามทุกข์ร้อน

2ฉะนั้นเราจะไม่กลัว ถึงแม้โลกจะสั่นสะเทือน

และภูเขาทลายราบลงสู่ใจกลางทะเล

3ถึงแม้มหาสมุทรคำรามก้องและซัดคลื่นเป็นฟองฟูฟ่อง

และภูเขาสะเทือนเลื่อนลั่น

เสลาห์

4มีแม่น้ำสายหนึ่งที่ให้ความยินดีแก่นครของพระเจ้า

ซึ่งเป็นที่ประทับบริสุทธิ์ขององค์ผู้สูงสุด

5พระเจ้าสถิตในนคร นครนั้นจะไม่ล่มสลาย

พระเจ้าจะทรงช่วยในยามรุ่งอรุณ

6ประชาชาติทั้งหลายโกลาหลอลหม่าน อาณาจักรต่างๆ ล่มสลาย

พระเจ้าทรงเปล่งพระสุรเสียง แผ่นดินโลกก็หลอมละลายไป

7พระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์สถิตกับเรา

พระเจ้าของยาโคบทรงเป็นป้อมปราการของเรา

เสลาห์

8มาเถิด มาดูพระราชกิจขององค์พระผู้เป็นเจ้า

ดูความเริศร้างที่พระองค์ทรงนำมาสู่โลก

9พระองค์ทรงกระทำให้สงครามยุติทั่วโลก

ทรงหักคันธนู และทำให้หอกหักสะบั้น

พระองค์ทรงเผาโล่46:9 หรือรถม้าศึก

10“จงนิ่งสงบและรู้ว่าเราเป็นพระเจ้า

เราจะได้รับการยกย่องท่ามกลางประชาชาติ

เราจะได้รับการยกย่องในโลก”

11พระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์สถิตกับเรา

พระเจ้าของยาโคบทรงเป็นป้อมปราการของเรา

เสลาห์