መዝሙር 45 – NASV & NSP

New Amharic Standard Version

መዝሙር 45:1-17

መዝሙር 45

የንጉሣዊ ሰርግ መዝሙር

ለመዘምራን አለቃ፤ “በጽጌረዳ” ዜማ፤ የቆሬ ልጆች ትምህርት፤ የፍቅር መዝሙር45 የሥነ ጽሑፉን ቅርጽ ወይም የመዝሙሩን ሁኔታ የሚያሳይ ሊሆን ይችላል።

1ልቤ መልካም ሐሳብ አፈለቀ፤

የተቀኘሁትን ቅኔ ለንጉሥ አሰማለሁ፤

አንደበቴም እንደ ባለሙያ ጸሓፊ ብርዕ ነው።

2አንተ ከሰዎች ሁሉ ይልቅ ውብ ነህ፤

ከንፈሮችህም የጸጋ ቃል ያፈልቃሉ፤

ስለዚህ እግዚአብሔር ለዘላለም ባርኮሃል።

3ኀያል ሆይ፤ ሰይፍህን በወገብህ ታጠቅ፤

ግርማ ሞገስንም ተላበስ።

4ስለ እውነት፣ ስለ ትሕትና፣ ስለ ጽድቅ

ሞገስን ተጐናጽፈህ በድል አድራጊነት ገሥግሥ፤

ቀኝ እጅህም ድንቅ ተግባር ታሳይ።

5የሾሉ ፍላጻዎችህ በንጉሥ ጠላቶች ልብ ይሰካሉ፤

ሕዝቦችም ከእግርህ በታች ይወድቃሉ።

6አምላክ ሆይ፤ ዙፋንህ ከዘላለም እስከ ዘላለም ይኖራል፤

የመንግሥትህ በትር የቅንነት በትር ናት።

7ጽድቅን ወደድህ፤ ዐመፃን ጠላህ፤

ስለዚህ እግዚአብሔር አምላክህ፣

ከጓደኞችህ ይልቅ አንተን የደስታ ዘይት ቀባህ።

8ልብስህ ሁሉ በከርቤ፣ በአደስና በጥንጁት መዐዛ ያውዳል፤

በዝኆን ጥርስ ከተዋቡ ቤተ መንግሥቶችም፣

የበገናና የመሰንቆ ድምፅ ደስ ያሰኙሃል።

9ከተከበሩት ሴቶችህ መካከል የነገሥታት ሴቶች ልጆች ይገኛሉ፤

ንግሥቲቱም በኦፊር ወርቅ አጊጣ በቀኝህ ቆማለች።

10ልጄ ሆይ፤ አድምጪ፤ አስተውዪ፤ ጆሮሽንም አዘንብዪ፤

ሕዝብሽንና የአባትሽን ቤት እርሺ።

11ንጉሥ በውበትሽ ተማርኳል፤

ጌታሽ ነውና አክብሪው።

12የጢሮስ ሴት ልጅ እጅ መንሻ ይዛ ትመጣለች፤45፥12 ወይም፣ የጢሮሳውያን ልብሰ ተክህኖ ከስጦታዎቹ መካከል አለ

ሀብታሞችም ደጅ ይጠኑሻል።

13የንጉሥ ልጅ ከላይ እስከ ታች ተሸልማ እልፍኟ ውስጥ አለች፤

ልብሷም ወርቀ ዘቦ ነው።

14በጥልፍ ሥራ ባጌጠ ልብስ ወደ ንጉሥ ትወሰዳለች፤

ደናግል ጓደኞቿም ተከትለዋት፣

ወደ አንተ ይመጣሉ።

15በደስታና በሐሤት ወደ ውስጥ ይመሯቸዋል፤

ወደ ንጉሡም ቤተ መንግሥት ይገባሉ።

16ወንዶች ልጆችህ በአባቶችህ እግር ይተካሉ፤

ገዦችም አድርገሽ በምድር ሁሉ ትሾሚያቸዋለሽ።

17ስምሽን በትውልድ ሁሉ ዘንድ መታሰቢያ አደርጋለሁ፤

ስለዚህ ሕዝቦች ከዘላለም እስከ ዘላለም ያወድሱሃል።

New Serbian Translation

Псалми 45:1-17

Псалам 45

За хоровођу, по напеву „Љиљани“, синова Корејевих. Поука. Песма љубави.

1Из срца ми теку речи умилне,

цару управљам своје стихове;

језик је мој писаљка хитрога писара.

2Ти си лепши од свих потомака људи,

с твојих уста милост се прелива,

јер Бог те је благословио довека.

3Уз бок припаши мач свој, јуначе,

у сјају и величанству своме.

4Изјаши победнички у величанству своме,

за истину, кроткост и праведност;

нек десница твоја страшна дела покаже.

5Нек стреле твоје зашиљене

пробију срце царевих душмана,

и народи нек падају под ноге твоје.

6Твој је престо, Боже, у веке векова!

Жезло је правде жезло твога царства.

7Волиш правду, а мрзиш неправду.

Зато те је Бог, твој Бог,

помазао уљем радости,

више него твоје другове;

8Сва ти одећа мирише на смирну, алоју и касију,

из дворова од слоноваче харфом те веселе.

9Ћерке царске твоје су дворкиње,

с десна ти царица стоји у офирском злату.

10Послушај, ћерко, погледај, добро слушај,

заборави народ свој и дом оца свог.

11Кад цар пожели лепоту твоју,

поклони му се, јер он је господар твој.

12Ћерка тирска доћи ће ти с даром,

богати људи тражиће твоју наклоност.

13Сва славна, ћерка царева чека у соби,

у хаљини златом извезеној,

14да је украшену доведу пред цара,

Девице је прате, другарице њене,

да и њих доведу пред тебе.

15Доводе их радосно, с весељем,

те ступају у цареве дворе.

16Твоји синови заузеће место очева твојих,

поставићеш их за кнезове по свој земљи.

17Име ћу ти овековечити кроз сва поколења;

зато ће те народи славити у веке векова.