መዝሙር 40 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 40:1-17

መዝሙር 40

የምስጋናና የርዳታ ልመና ጸሎት

40፥13-17 ተጓ ምብ – መዝ 70፥1-5

ለመዘምራን አለቃ፤ የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔርን ደጅ ጠናሁት፤

እርሱም ዘንበል አለልኝ፤ ጩኸቴንም ሰማ።

2ከሚውጥ ጕድጓድ፣

ከሚያዘቅጥ ማጥ አወጣኝ፤

እግሮቼን በዐለት ላይ አቆመ፤

አካሄዴንም አጸና።

3ለአምላካችን የሚሆን ውዳሴ፣

አዲስ ዝማሬን በአፌ ላይ አኖረ፤

ብዙዎች ያያሉ፤ ይፈራሉም፤

በእግዚአብሔር ይታመናሉ።

4እግዚአብሔርን መታመኛው ያደረገ፣

ወደ ትዕቢተኞች የማይመለከት፣

የሐሰት አማልክትን40፥4 ወይም ሐሰትን ወደሚከተሉት ተብሎ መተርጐም ይችላል። ወደሚከተሉት የማያይ

ሰው ብፁዕ ነው።

5እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ፤

አንተ ያደረግኸው ድንቅ ነገር ብዙ ነው፤

ለእኛ ያቀድኸውን፣

ሊዘረዝርልህ የሚችል ማንም የለም፤

ላውራው ልናገረው ብል፣

ስፍር ቍጥር አይኖረውም።

6መሥዋዕትንና ቊርባንን አልፈለግህም፤

ጆሮዎቼን ግን ከፈትህ፤40፥6 ዕብራይስጡ ከዚህ ጋር ይስማማል፤ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም ግን፣ አካልን ግን አዘጋጀህልኝ ይላል።

የሚቃጠል መሥዋዕትን፣

የኀጢአትንም መሥዋዕት አልሻህም።

7እኔም እንዲህ አልሁ፤ “እነሆ፤ መጥቻለሁ፤

ስለ እኔ በመጽሐፍ ተጽፏል፤

8አምላኬ ሆይ፤ ፈቃድህን ላደርግ እሻለሁ፤

ሕግህም በልቤ ውስጥ አለ።”

9በታላቅ ጉባኤ ውስጥ ጽድቅን አበሠርሁ፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ እንደምታውቀው፣

ከንፈሮቼን አልገጠምሁም።

10ጽድቅህን በልቤ አልሸሸግሁም፤

ታማኝነትህንና ማዳንህን እናገራለሁ፤

ምሕረትህንና እውነትህን፣

ከታላቅ ጉባኤ አልደበቅሁም።

11እግዚአብሔር ሆይ፤ ምሕረትህን አትንፈገኝ፤

ቸርነትህና እውነትህ ዘወትር ይጠብቁኝ፤

12ስፍር ቍጥር የሌለው ክፋት ከብቦኛልና፤

የኀጢአቴ ብዛት ስለ ያዘኝ ማየት ተስኖኛል፤

ከራሴ ጠጕር ይልቅ በዝቷል፤

ልቤም ከድቶኛል።

13እግዚአብሔር ሆይ፤ ታድነኝ ዘንድ ፈቃድህ ይሁን፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ እኔን ለመርዳት ፍጠን።

14ነፍሴን ለመንጠቅ የሚፈልጉ

ይፈሩ፤ ይዋረዱም፤

ጕዳቴንም የሚሹ፣

ተዋርደው በመጡበት ይመለሱ።

15በእኔ ላይ፣ “ዕሠይ! ዕሠይ!” የሚሉ፣

በራሳቸው ዕፍረት ይደንግጡ።

16አንተን የሚፈልጉ ሁሉ ግን፣

ሐሤት ያድርጉ፤ በአንተም ደስ ይበላቸው፤

ዘወትር የአንተን ማዳን የሚወድዱ፣

እግዚአብሔር ከፍ ከፍ ይበል” ይበሉ።

17እኔ ድኻና ችግረኛ ነኝ፤

ጌታ ግን ያስብልኛል።

አንተ ረዳቴና አዳኜ ነህ፤

አምላኬ ሆይ፤ አትዘግይ።

Ketab El Hayat

مزمور 40:1-17

الْمَزْمُورُ الأَرْبَعُونَ

لِقَائِدِ الْمُنْشِدِينَ، مَزْمُورٌ لِدَاوُدَ

1انْتَظَرْتُ الرَّبَّ صَابِراً، فَالْتَفَتَ إِلَيَّ وَسَمِعَ صُرَاخَ اسْتِغَاثَتِي، 2وَانْتَشَلَنِي مِنْ هُوَّةِ الْهَلاكِ، مِنْ طِينِ الْمُسْتَنْقَعِ. وَأَوْقَفَ قَدَمَيَّ عَلَى أَرْضٍ صَخْرِيَّةٍ، فَصِرْتُ أَمْشِي بِخُطُوَاتٍ ثَابِتَةٍ. 3وَضَعَ فِي فَمِي تَرْنِيمَةً جَدِيدَةً، قَصِيدَةَ تَسْبِيحٍ لإِلَهِنَا. يَرَى ذَلِكَ كَثِيرُونَ فَيَخَافُونَ الرَّبَّ.

4طُوبَى لِرَجُلٍ وَضَعَ فِي الرَّبِّ ثِقَتَهُ، وَلَمْ يَلْتَفِتْ إِلَى الْمُتَكَبِّرِينَ وَالْمُنْحَرِفِينَ إِلَى الْكَذِبِ. 5أَيُّهَا الرَّبُّ إِلَهِي، مَا أَكْثَرَ أَعْمَالَكَ الْعَجِيبَةَ! إِنْ تَحَدَّثْتُ عَنْ خُطَطِكَ الرَّائِعَةِ لَنَا فَلَنْ أَقْدِرَ أَنْ أُحْصِيَهَا. زَادَتْ عَنْ أَنْ تُعَدَّ. 6لَمْ تُرِدْ أَوْ تَطْلُبْ ذَبَائِحَ وَمُحْرَقَاتٍ عَنِ الْخَطِيئَةِ، لَكِنَّكَ وَهَبْتَنِي أُذُنَيْنِ مُصْغِيَتَيْنِ مُطِيعَتَيْنِ. 7عِنْدَئِذٍ قُلْتُ: «هَا أَنَا أَجِيءُ، كَمَا هُوَ مَكْتُوبٌ عَنِّي فِي دَرْجِ الْكِتَابِ: 8إِنَّ مَسَرَّتِي أَنْ أَعْمَلَ مَشِيئَتَكَ الصَّالِحَةَ يَا إِلَهِي، وَشَرِيعَتُكَ فِي صَمِيمِ قَلْبِي. 9أَعْلَنْتُ بِرَّكَ وَسَطَ جَمَاعَةِ شَعْبِكَ الْعَظِيمِ، وَأَنْتَ يَا رَبُّ عَلِمْتَ أَنَّنِي لَمْ أُلْجِمْ شَفَتَيَّ. 10لَمْ أُخْفِ بِرَّكَ دَاخِلَ قَلْبِي، بَلْ أَعْلَنْتُ أَمَانَتَكَ وَخَلاصَكَ. لَمْ أَكْتُمْ رَحْمَتَكَ وَحَقَّكَ عَنْ جَمَاعَةِ شَعْبِكَ الْعَظِيمِ».

11فَأَنْتَ يَا رَبُّ لَنْ تَمْنَعَ مَرَاحِمَكَ عَنِّي. تَنْصُرُنِي دَائِماً رَحْمَتُكَ وَحَقُّكَ. 12إِنَّ شُرُوراً لَا تُحْصَى قَدْ أَحَاطَتْ بِي، وَآثَامِي قَدْ أَطْبَقَتْ عَلَيَّ فَأَعْمَتْنِي لأَنَّهَا أَكْثَرُ مِنْ شَعْرِ رَأْسِي، وَقَلْبِي قَدْ خَذَلَنِي. 13يَا رَبُّ، ارْتَضِ أَنْ تُنَجِّيَنِي. أَسْرِعْ يَا رَبُّ لإِغَاثَتِي. 14لِيَخْزَ وَلْيَخْجَلْ مَعاً الَّذِينَ يَسْعَوْنَ إِلَى قَتْلِي. لِيُدْبِرْ وَلْيَخْزَ الْمَسْرُورُونَ بِأَذِيَّتِي. 15لِيَذْهَلْ خِزْياً السَّاخِرُونَ مِنِّي. 16وَلْيَفْرَحْ وَيَبْتَهِجْ بِكَ جَمِيعُ طَالِبِيكَ، وَلْيَقُلْ كُلَّ حِينٍ مُحبُّو خَلاصِكَ: «يَتَعَظَّمُ الرَّبُّ». 17أَمَّا أَنَا فَمِسْكِينٌ وَبَائِسٌ. الرَّبُّ يَهْتَمُّ بِي. عَوْنِي وَمُنْقِذِي أَنْتَ. فَلَا تَتَوَانَ يَا إِلَهِي.