መዝሙር 40 – NASV & KJV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 40:1-17

መዝሙር 40

የምስጋናና የርዳታ ልመና ጸሎት

40፥13-17 ተጓ ምብ – መዝ 70፥1-5

ለመዘምራን አለቃ፤ የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔርን ደጅ ጠናሁት፤

እርሱም ዘንበል አለልኝ፤ ጩኸቴንም ሰማ።

2ከሚውጥ ጕድጓድ፣

ከሚያዘቅጥ ማጥ አወጣኝ፤

እግሮቼን በዐለት ላይ አቆመ፤

አካሄዴንም አጸና።

3ለአምላካችን የሚሆን ውዳሴ፣

አዲስ ዝማሬን በአፌ ላይ አኖረ፤

ብዙዎች ያያሉ፤ ይፈራሉም፤

በእግዚአብሔር ይታመናሉ።

4እግዚአብሔርን መታመኛው ያደረገ፣

ወደ ትዕቢተኞች የማይመለከት፣

የሐሰት አማልክትን40፥4 ወይም ሐሰትን ወደሚከተሉት ተብሎ መተርጐም ይችላል። ወደሚከተሉት የማያይ

ሰው ብፁዕ ነው።

5እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ፤

አንተ ያደረግኸው ድንቅ ነገር ብዙ ነው፤

ለእኛ ያቀድኸውን፣

ሊዘረዝርልህ የሚችል ማንም የለም፤

ላውራው ልናገረው ብል፣

ስፍር ቍጥር አይኖረውም።

6መሥዋዕትንና ቊርባንን አልፈለግህም፤

ጆሮዎቼን ግን ከፈትህ፤40፥6 ዕብራይስጡ ከዚህ ጋር ይስማማል፤ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም ግን፣ አካልን ግን አዘጋጀህልኝ ይላል።

የሚቃጠል መሥዋዕትን፣

የኀጢአትንም መሥዋዕት አልሻህም።

7እኔም እንዲህ አልሁ፤ “እነሆ፤ መጥቻለሁ፤

ስለ እኔ በመጽሐፍ ተጽፏል፤

8አምላኬ ሆይ፤ ፈቃድህን ላደርግ እሻለሁ፤

ሕግህም በልቤ ውስጥ አለ።”

9በታላቅ ጉባኤ ውስጥ ጽድቅን አበሠርሁ፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ እንደምታውቀው፣

ከንፈሮቼን አልገጠምሁም።

10ጽድቅህን በልቤ አልሸሸግሁም፤

ታማኝነትህንና ማዳንህን እናገራለሁ፤

ምሕረትህንና እውነትህን፣

ከታላቅ ጉባኤ አልደበቅሁም።

11እግዚአብሔር ሆይ፤ ምሕረትህን አትንፈገኝ፤

ቸርነትህና እውነትህ ዘወትር ይጠብቁኝ፤

12ስፍር ቍጥር የሌለው ክፋት ከብቦኛልና፤

የኀጢአቴ ብዛት ስለ ያዘኝ ማየት ተስኖኛል፤

ከራሴ ጠጕር ይልቅ በዝቷል፤

ልቤም ከድቶኛል።

13እግዚአብሔር ሆይ፤ ታድነኝ ዘንድ ፈቃድህ ይሁን፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ እኔን ለመርዳት ፍጠን።

14ነፍሴን ለመንጠቅ የሚፈልጉ

ይፈሩ፤ ይዋረዱም፤

ጕዳቴንም የሚሹ፣

ተዋርደው በመጡበት ይመለሱ።

15በእኔ ላይ፣ “ዕሠይ! ዕሠይ!” የሚሉ፣

በራሳቸው ዕፍረት ይደንግጡ።

16አንተን የሚፈልጉ ሁሉ ግን፣

ሐሤት ያድርጉ፤ በአንተም ደስ ይበላቸው፤

ዘወትር የአንተን ማዳን የሚወድዱ፣

እግዚአብሔር ከፍ ከፍ ይበል” ይበሉ።

17እኔ ድኻና ችግረኛ ነኝ፤

ጌታ ግን ያስብልኛል።

አንተ ረዳቴና አዳኜ ነህ፤

አምላኬ ሆይ፤ አትዘግይ።

King James Version

Psalms 40:1-17

To the chief Musician, A Psalm of David.

1I waited patiently for the LORD; and he inclined unto me, and heard my cry.40.1 I waited…: Heb. In waiting I waited

2He brought me up also out of an horrible pit, out of the miry clay, and set my feet upon a rock, and established my goings.40.2 an…: Heb. a pit of noise

3And he hath put a new song in my mouth, even praise unto our God: many shall see it, and fear, and shall trust in the LORD.

4Blessed is that man that maketh the LORD his trust, and respecteth not the proud, nor such as turn aside to lies.

5Many, O LORD my God, are thy wonderful works which thou hast done, and thy thoughts which are to us-ward: they cannot be reckoned up in order unto thee: if I would declare and speak of them, they are more than can be numbered.40.5 they cannot…: or, none can order them unto thee

6Sacrifice and offering thou didst not desire; mine ears hast thou opened: burnt offering and sin offering hast thou not required.40.6 opened: Heb. digged

7Then said I, Lo, I come: in the volume of the book it is written of me,

8I delight to do thy will, O my God: yea, thy law is within my heart.40.8 within…: Heb. in the midst of my bowels

9I have preached righteousness in the great congregation: lo, I have not refrained my lips, O LORD, thou knowest.

10I have not hid thy righteousness within my heart; I have declared thy faithfulness and thy salvation: I have not concealed thy lovingkindness and thy truth from the great congregation.

11Withhold not thou thy tender mercies from me, O LORD: let thy lovingkindness and thy truth continually preserve me.

12For innumerable evils have compassed me about: mine iniquities have taken hold upon me, so that I am not able to look up; they are more than the hairs of mine head: therefore my heart faileth me.40.12 faileth: Heb. forsaketh

13Be pleased, O LORD, to deliver me: O LORD, make haste to help me.

14Let them be ashamed and confounded together that seek after my soul to destroy it; let them be driven backward and put to shame that wish me evil.

15Let them be desolate for a reward of their shame that say unto me, Aha, aha.

16Let all those that seek thee rejoice and be glad in thee: let such as love thy salvation say continually, The LORD be magnified.

17But I am poor and needy; yet the Lord thinketh upon me: thou art my help and my deliverer; make no tarrying, O my God.