መዝሙር 40 – NASV & CARST

New Amharic Standard Version

መዝሙር 40:1-17

መዝሙር 40

የምስጋናና የርዳታ ልመና ጸሎት

40፥13-17 ተጓ ምብ – መዝ 70፥1-5

ለመዘምራን አለቃ፤ የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔርን ደጅ ጠናሁት፤

እርሱም ዘንበል አለልኝ፤ ጩኸቴንም ሰማ።

2ከሚውጥ ጕድጓድ፣

ከሚያዘቅጥ ማጥ አወጣኝ፤

እግሮቼን በዐለት ላይ አቆመ፤

አካሄዴንም አጸና።

3ለአምላካችን የሚሆን ውዳሴ፣

አዲስ ዝማሬን በአፌ ላይ አኖረ፤

ብዙዎች ያያሉ፤ ይፈራሉም፤

በእግዚአብሔር ይታመናሉ።

4እግዚአብሔርን መታመኛው ያደረገ፣

ወደ ትዕቢተኞች የማይመለከት፣

የሐሰት አማልክትን40፥4 ወይም ሐሰትን ወደሚከተሉት ተብሎ መተርጐም ይችላል። ወደሚከተሉት የማያይ

ሰው ብፁዕ ነው።

5እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ፤

አንተ ያደረግኸው ድንቅ ነገር ብዙ ነው፤

ለእኛ ያቀድኸውን፣

ሊዘረዝርልህ የሚችል ማንም የለም፤

ላውራው ልናገረው ብል፣

ስፍር ቍጥር አይኖረውም።

6መሥዋዕትንና ቊርባንን አልፈለግህም፤

ጆሮዎቼን ግን ከፈትህ፤40፥6 ዕብራይስጡ ከዚህ ጋር ይስማማል፤ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም ግን፣ አካልን ግን አዘጋጀህልኝ ይላል።

የሚቃጠል መሥዋዕትን፣

የኀጢአትንም መሥዋዕት አልሻህም።

7እኔም እንዲህ አልሁ፤ “እነሆ፤ መጥቻለሁ፤

ስለ እኔ በመጽሐፍ ተጽፏል፤

8አምላኬ ሆይ፤ ፈቃድህን ላደርግ እሻለሁ፤

ሕግህም በልቤ ውስጥ አለ።”

9በታላቅ ጉባኤ ውስጥ ጽድቅን አበሠርሁ፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ እንደምታውቀው፣

ከንፈሮቼን አልገጠምሁም።

10ጽድቅህን በልቤ አልሸሸግሁም፤

ታማኝነትህንና ማዳንህን እናገራለሁ፤

ምሕረትህንና እውነትህን፣

ከታላቅ ጉባኤ አልደበቅሁም።

11እግዚአብሔር ሆይ፤ ምሕረትህን አትንፈገኝ፤

ቸርነትህና እውነትህ ዘወትር ይጠብቁኝ፤

12ስፍር ቍጥር የሌለው ክፋት ከብቦኛልና፤

የኀጢአቴ ብዛት ስለ ያዘኝ ማየት ተስኖኛል፤

ከራሴ ጠጕር ይልቅ በዝቷል፤

ልቤም ከድቶኛል።

13እግዚአብሔር ሆይ፤ ታድነኝ ዘንድ ፈቃድህ ይሁን፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ እኔን ለመርዳት ፍጠን።

14ነፍሴን ለመንጠቅ የሚፈልጉ

ይፈሩ፤ ይዋረዱም፤

ጕዳቴንም የሚሹ፣

ተዋርደው በመጡበት ይመለሱ።

15በእኔ ላይ፣ “ዕሠይ! ዕሠይ!” የሚሉ፣

በራሳቸው ዕፍረት ይደንግጡ።

16አንተን የሚፈልጉ ሁሉ ግን፣

ሐሤት ያድርጉ፤ በአንተም ደስ ይበላቸው፤

ዘወትር የአንተን ማዳን የሚወድዱ፣

እግዚአብሔር ከፍ ከፍ ይበል” ይበሉ።

17እኔ ድኻና ችግረኛ ነኝ፤

ጌታ ግን ያስብልኛል።

አንተ ረዳቴና አዳኜ ነህ፤

አምላኬ ሆይ፤ አትዘግይ።

Священное Писание (Восточный перевод), версия для Таджикистана

Забур 40:1-14

Песнь 40

1Дирижёру хора. Песнь Довуда.

2Благословен тот, кто заботится о слабом40:2 Или: «о бедном».:

во время беды избавит его Вечный.

3Вечный сохранит его и сбережёт ему жизнь,

счастьем одарит его на земле

и не отдаст его на произвол врагов.

4Вечный укрепит его во время болезни

и поднимет его с ложа недуга.

5Я сказал: «Вечный, помилуй меня;

исцели меня – я пред Тобой согрешил».

6Враги мои со злобой говорят обо мне:

«Когда же умрёт он и погибнет имя его?»

7Если приходит кто навестить меня,

то ложь говорит, а в сердце своём слагает злые слухи;

потом он выходит и всем их рассказывает.

8Все враги мои шепчутся против меня,

думают худшее обо мне40:8 Или: «зло замышляют против меня».:

9«Смертельный недуг его одолел;

он слёг и больше ему не встать».

10Даже близкий друг, на которого я полагался,

тот, кто ел мой хлеб,

пошёл против меня40:10 См. Ин. 13:18, 21-27..

11Но Ты, Вечный, помилуй меня;

подними меня, и я воздам им!

12Из того я узнаю, что угоден Тебе,

если не одолеет меня враг мой,

13а меня Ты поддержишь за непорочность мою

и навеки поставишь пред Собою.

Заключительное благословение первой книги

14Хвала Вечному, Богу Исроила,

от века и до века!

Аминь и аминь!