መዝሙር 4 – NASV & NIV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 4:1-8

መዝሙር 4

የሠርክ ጸሎት

ለመዘምራን አለቃ፤ በበገናዎች የሚዜም የዳዊት መዝሙር።

1የጽድቄ አምላክ ሆይ፤

በጠራሁህ ጊዜ መልስልኝ፤

ከጭንቀቴ አሳርፈኝ፤

ማረኝ፤ ጸሎቴንም ስማ።

2ሰዎች ሆይ፤ እስከ መቼ ድረስ ክብሬን ዝቅ4፥2 ወይም ወደ ራሳችሁ ታደርጋላችሁ?

እስከ መቼስ ድረስ ከንቱ ነገርን ትወድዳላችሁ? ሐሰትንስ4፥2 ወይም የሐሰት አማልክት ትሻላችሁ? ሴላ

3እግዚአብሔር ጻድቁን ለራሱ እንደ ለየ ዕወቁ፤

እግዚአብሔር ወደ እርሱ በተጣራሁ ጊዜ ይሰማኛል።

4ስትቈጡ ኀጢአት አትሥሩ፤

በዐልጋችሁም ላይ ሳላችሁ፣

ልባችሁን መርምሩ፤ ጸጥም በሉ። ሴላ

5የጽድቅን መሥዋዕት አቅርቡ፤

በእግዚአብሔርም ታመኑ።

6ብዙዎች፣ “አንዳች በጎ ነገር ማን ያሳየናል?” ይላሉ፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ የፊትህ ብርሃን በላያችን ይብራ።

7ስንዴና አዲስ የወይን ጠጅ በብዛት ባመረቱ ጊዜ ከሚያገኙት ደስታ ይልቅ፣

አንተ ልቤን በታላቅ ሐሤት ሞልተኸዋል።

8በሰላም እተኛለሁ፤ አንቀላፋለሁም፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ ያለ ሥጋት የምታሳድረኝ አንተ ብቻ ነህና።

New International Version

Psalms 4:1-8

Psalm 4In Hebrew texts 4:1-8 is numbered 4:2-9.

For the director of music. With stringed instruments. A psalm of David.

1Answer me when I call to you,

my righteous God.

Give me relief from my distress;

have mercy on me and hear my prayer.

2How long will you people turn my glory into shame?

How long will you love delusions and seek false gods4:2 Or seek lies?4:2 The Hebrew has Selah (a word of uncertain meaning) here and at the end of verse 4.

3Know that the Lord has set apart his faithful servant for himself;

the Lord hears when I call to him.

4Tremble and4:4 Or In your anger (see Septuagint) do not sin;

when you are on your beds,

search your hearts and be silent.

5Offer the sacrifices of the righteous

and trust in the Lord.

6Many, Lord, are asking, “Who will bring us prosperity?”

Let the light of your face shine on us.

7Fill my heart with joy

when their grain and new wine abound.

8In peace I will lie down and sleep,

for you alone, Lord,

make me dwell in safety.