መዝሙር 39 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 39:1-13

መዝሙር 39

ታላቅ እግዚአብሔር-ታናሽ ሰው

ለመዘምራን አለቃ፣ ለኤዶታም፤ የዳዊት መዝሙር።

1እኔ፣ “በአንደበቴ እንዳልበድል፣

መንገዴን እጠብቃለሁ፤

ክፉዎችም በእኔ ዘንድ እስካሉ ድረስ፣

ልጓም በአፌ አስገባለሁ” አልሁ።

2እንደ ዲዳ ዝም አልሁ፤

ለበጎ ነገር እንኳ አፌን ዘጋሁ፤

ሆኖም ጭንቀቴ ባሰ።

3ልቤ በውስጤ ጋለ፤

በማሰላስልበትም ጊዜ እሳቱ ነደደ፤

ከዚያም በአንደበቴ እንዲህ ተናገርሁ፤

4እግዚአብሔር ሆይ፤ የሕይወቴን ፍጻሜ፣

የዘመኔንም ቍጥር አስታውቀኝ፤

ዐላፊ ጠፊ መሆኑንም ልረዳ።

5እነሆ፤ ዘመኔን በስንዝር ለክተህ አስቀመጥህ፤

ዕድሜዬም በፊትህ እንደ ኢምንት ነው፤

በርግጥ የሰው ሁሉ ሕይወት ተን ነው። ሴላ

6“ሰው የጥላ ውልብታ ነው፤

በከንቱም ይታወካል፤

ለማን እንደሚሆን ሳያውቅ ሀብት ንብረት ያከማቻል።

7“ጌታ ሆይ፤ አሁንስ ወደ ማን ልመልከት?

ተስፋዬ በአንተ ላይ ነው።

8ከኀጢአቴ ሁሉ አድነኝ፤

የሰነፎች መሣለቂያ አታድርገኝ።

9ይህን ያደረግህ አንተ ነህና፣

ዝም እላለሁ፤ አፌንም አልከፍትም።

10ክንድህን አንሣልኝ፤

ከእጅህ ምት የተነሣ ደክሜአለሁ።

11ሰዎችን ስለ ኀጢአታቸው ለመቅጣት ትገሥጻቸዋለህ፤

ሀብታቸውንም ብል እንደ በላው ታደርጋለህ፤

በርግጥ ሰው ሁሉ ተን ብቻ ነው። ሴላ

12እግዚአብሔር ሆይ፤ ጸሎቴን ስማ፤

ጩኸቴን አድምጥ፤

ልቅሶዬንም ቸል አትበል፤

በአንተ ፊት እኔ መጻተኛ ነኝና፤

እንደ አባቶቼም እንግዳ ነኝ።

13ላለመመለስ ከመሰናበቴ በፊት፣

ዳግመኛ ደስ ይለኝ ዘንድ ዐይንህን ከላዬ አንሣ።”

Ketab El Hayat

مزمور 39:1-13

الْمَزْمُورُ التَّاسِعُ والثَّلاثُونَ

لِقَائِدِ الْمُنْشِدِينَ، مَزْمُورٌ لِدَاوُدَ

1قُلْتُ: «أَحْرِصُ عَلَى حُسْنِ الْمَسْلَكِ فَلَا يُخْطِئُ لِسَانِي الْقَوْلَ. سَأَكُمُّ فَمِي عَنِ الْكَلامِ مَادَامَ الشِّرِّيرُ أَمَامِي». 2صَمَتُّ صَمْتاً. أَمْسَكْتُ حَتَّى عَنِ الْخَيْرِ، فَثَارَ وَجَعِي. 3الْتَهَبَ قَلْبِي فِي دَاخِلِي، وَفِي تَأَمُّلِي اشْتَعَلَتْ فِيَّ النَّارُ، فَأَطْلَقْتُ لِسَانِي بِالْكَلامِ. 4يَا رَبُّ عَرِّفْنِي مَتَى تَكُونُ نِهَايَتِي، وَكَمْ تَطُولُ أَيَّامِي فَأُدْرِكَ أَنَّنِي إِنْسَانٌ زَائِلٌ. 5هُوَذَا قَدْ جَعَلْتَ حَيَاتِي قَصِيرَةً، وَعُمْرِي كَلَا شَيْءَ أَمَامَكَ. كُلُّ إِنْسَانٍ حَيٍّ لَيْسَ سِوَى نَفْخَةٍ! 6إِنَّمَا كَخَيَالٍ يَتَمَشَّى الإِنْسَانُ، فَعَبَثاً يُكَافِحُ النَّاسُ. يَجْمَعُ الْوَاحِدُ مِنْهُمْ ثَرْوَةً وَلَا يَدْرِي مَنْ يَرِثُهَا مِنْ بَعْدِهِ.

7وَالآنَ، فَأَيُّ شَيْءٍ أَنْتَظِرُ يَا رَبُّ؟ إِنَّمَا فِيكَ رَجَائِي. 8نَجِّنِي مِنْ جَمِيعِ مَعَاصِيَّ، وَلَا تَجْعَلْنِي عَاراً عِنْدَ الأَحْمَقِ. 9صَمَتُّ. لَا أَفْتَحُ فَمِي، لأَنَّكَ أَنْتَ فَعَلْتَ هَذَا. 10ارْفَعْ عَنِّي ضَرْبَتَكَ فَقَدْ فَنِيْتُ مِنْ صَفْعَةِ يَدِكَ. 11عِنْدَمَا تُؤَدِّبُ الإِنْسَانَ بِالتَّوْبِيخِ عَلَى الإِثْمِ، تُتْلِفُ بَهَاءَهُ إِتْلافَ الْعُثِّ. إِنَّمَا كُلُّ إِنْسَانٍ نَفْخَةٌ. 12يَا رَبُّ اسْمَعْ صَلاتِي. وَأَصْغِ إِلَى صُرَاخِي، وَلَا تَسْكُتْ أَمَامَ دُمُوعِي، لأَنِّي غَرِيبٌ عِنْدَكَ وَعَابِرُ سَبِيلٍ كَجَمِيعِ آبَائِي. 13حَوِّلْ غَضَبَكَ عَنِّي فَأَنْتَعِشَ، قَبْلَ أَنْ أَمُوتَ وَيَخْتَفِيَ أَثَرِي.