መዝሙር 34 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 34:1-22

መዝሙር 3434 34 የዚህ መዝሙር እያንዳንዱ ጥቅስ ተከታታይ ፊደላት ባሉት የዕብራይስጥ ሆህያት የሚጀመር ሲሆን፣ ጅማሬው ወይም ጅማሬውና መጨረሻው ትርጕም የሚሰጥ ግጥም ነው።

የእግዚአብሔር ፍትሕ ውዳሴ

እንደ እብድ ሆኖ አቤሜሌክ ፊት በመቅረቡ ተባርሮ በወጣ ጊዜ የዘመረው፤ የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔርን ሁልጊዜ እባርከዋለሁ፤

ምስጋናውም ዘወትር ከአፌ አይለይም።

2ነፍሴ በእግዚአብሔር ተመካች፤

ትሑታንም ይህን ሰምተው ሐሤት ያደርጋሉ።

3ኑና ከእኔ ጋር እግዚአብሔርን አክብሩት፤

ስሙንም በአንድነት ከፍ ከፍ እናድርግ።

4እግዚአብሔርን ፈለግሁት፤ እርሱም መለሰልኝ፤

ከፍርሀቴም ሁሉ አዳነኝ።

5ወደ እርሱ የሚመለከቱ ያበራሉ፤

ፊታቸውም ከቶ አያፍርም።

6ይህ ችግረኛ ጮኸ፤ እግዚአብሔርም ሰማው፤

ከመከራውም ሁሉ አዳነው።

7እግዚአብሔርን በሚፈሩት ዙሪያ የእግዚአብሔር መልአክ ይሰፍራል፤

ያድናቸዋልም።

8እግዚአብሔር ቸር መሆኑን ቀምሳችሁ እዩ፤

እርሱን መጠጊያ የሚያደርግ ምንኛ ቡሩክ ነው!

9እናንተ ቅዱሳኑ፤ እግዚአብሔርን ፍሩት፤

እርሱን የሚፈሩት አንዳች አያጡምና።

10አንበሶች ሊያጡ፣ ሊራቡም ይችላሉ፤

እግዚአብሔርን የሚሹ ግን መልካም ነገር አይጐድልባቸውም።

11ልጆቼ ሆይ፣ ኑ፤ ስሙኝ፤

እግዚአብሔርን መፍራት አስተምራችኋለሁ።

12ሕይወትን የሚወድድ፣

በጎውንም ያይ ዘንድ ዕድሜን የሚመኝ ማን ነው?

13አንደበትህን ከክፉ ነገር ከልክል፤

ከንፈርህንም ከሽንገላ ጠብቅ።

14ከክፉ ሽሽ፤ መልካሙንም አድርግ፤

ሰላምን ፈልጋት፤ ተከተላትም።

15የእግዚአብሔር ዐይኖች ወደ ጻድቃን ናቸው፤

ጆሮዎቹም ለጩኸታቸው ክፍት ናቸው።

16መታሰቢያቸውን ከምድር ለማጥፋት፣

የእግዚአብሔር ፊት በክፉ አድራጊዎች ላይ ነው።

17ጻድቃን ሲጮኹ፣ እግዚአብሔር ይሰማቸዋል፤

ከመከራቸውም ሁሉ ያድናቸዋል።

18እግዚአብሔር ልባቸው ለተሰበረ ቅርብ ነው፤

መንፈሳቸው የተሰበረውንም ያድናቸዋል።

19የጻድቅ መከራው ብዙ ነው፤

እግዚአብሔር ግን ከሁሉም ያድነዋል።

20ዐጥንቶቹን ሁሉ ይጠብቃል፤

ከእነርሱም አንድ አይሰበርም።

21ኀጢአተኞችን ክፋት ይገድላቸዋል፤

ጻድቃንን የሚጠሉ ይፈረድባቸዋል።

22እግዚአብሔር የባሪያዎቹን ነፍስ ይቤዣል፤

እርሱንም መጠጊያ ያደረገ አይፈረድበትም።

Ketab El Hayat

مزمور 34:1-22

الْمَزْمُورُ الرَّابِعُ وَالثَّلاثُونَ

لِدَاوُدَ عِنْدَمَا ادَّعَى الْجُنُونَ أَمَامَ أَبِيمَالِكَ، فَصَرَفَهُ عَنْهُ، فَمَضَى آمِناً.

1أُبَارِكُ الرَّبَّ فِي كُلِّ حِينٍ. تَسْبِيحُهُ دَائِماً فِي فَمِي. 2تَفْتَخِرُ نَفْسِي بِالرَّبِّ، فَيَسْمَعُنِي الْوُدَعَاءُ وَيَفْرَحُونَ. 3مَجِّدُوا الرَّبَّ مَعِي، وَلْنُعَظِّمِ اسْمَهُ مَعاً.

4الْتَمَسْتُ الرَّبَّ فَأَجَابَنِي، وأَنْقَذَنِي مِنْ كُلِّ مَخَاوِفِي. 5الَّذِينَ تَطَلَّعُوا إِلَيْهِ اسْتَنَارُوا، وَلَمْ تَخْجَلْ وُجُوهُهُمْ قَطُّ. 6هَذَا الْمِسْكِينُ اسْتَغَاثَ، فَسَمِعَهُ الرَّبُّ وَأَنْقَذَهُ مِنْ جَمِيعِ ضِيقَاتِهِ. 7مَلاكُ الرَّبِّ يُخَيِّمُ حَوْلَ خَائِفِيهِ، وَيُنَجِّيهِمْ. 8ذُوقُوا وَانْظُرُوا مَا أَطْيَبَ الرَّبَّ. طُوبَى لِلرَّجُلِ الْمُتَوَكِّلِ عَلَيْهِ. 9اتَّقُوا الرَّبَّ يَا قِدِّيسِيهِ، لأَنَّهُ لَيْسَ عَوَزٌ لِمُتَّقِيهِ. 10تَحْتَاجُ الأَشْبَالُ وَتَجُوعُ، وَأَمَّا طَالِبُو الرَّبِّ فَلَا يُعْوِزُهُمْ شَيْءٌ مِنَ الْخَيْرِ.

11تَعَالَوْا أَيُّهَا الْبَنُونَ وَأَصْغُوا إِلَيَّ، فَأُعَلِّمَكُمْ مَخَافَةَ الرَّبِّ. 12فَمَنْ أَرَادَ أَنْ يَتَمَتَّعَ بِحَيَاةٍ سَعِيدَةٍ وَأَيَّامٍ طَيِّبَةٍ، 13فَلْيَمْنَعْ لِسَانَهُ عَنِ الشَّرِّ وَشَفَتَيْهِ عَنْ كَلامِ الْغِشِّ 14لِيَتَحَوَّلْ عَنِ الشَّرِّ وَيَفْعَلِ الْخَيْرَ. لِيَطْلُبِ السَّلامَ وَيَسْعَ لِلْوُصُولِ إِلَيْهِ 15لأَنَّ الرَّبَّ يَرْعَى الأَبْرَارَ بِعِنَايَتِهِ وَيَسْتَجِيبُ إِلَى دُعَائِهِمْ. 16وَلَكِنْ يَقِفُ ضِدَّ الَّذِينَ يَعْمَلُونَ الشَّرَّ لِيَسْتَأْصِلَ مِنَ الأَرْضِ ذِكْرَهُمْ. 17يَسْتَغِيثُ الأَبْرَارُ، فَيَسْمَعُ لَهُمُ الرَّبُّ وَيُنْقِذُهُمْ مِنْ جَمِيعِ ضِيقَاتِهِمْ. 18الرَّبُّ قَرِيبٌ مِنْ مُنْكَسِرِي الْقَلْبِ، وَيُخَلِّصُ مُنْسَحِقِي الرُّوحِ. 19مَا أَكْثَرَ مَصَائِبَ الصِّدِّيقِ، وَلَكِنْ مِنْ جَمِيعِهَا يُنْقِذُهُ الرَّبُّ. 20يَحْفَظُ عِظَامَهُ كُلَّهَا، فَلَا تُكْسَرُ وَاحِدَةٌ مِنْهَا. 21الشَّرُّ يُمِيتُ الشِّرِّيرَ، وَالَّذِينَ يُبْغِضُونَ الصِّدِّيقَ يُعَاقَبُونَ. 22الرَّبُّ يَفْدِي نُفُوسَ عَبِيدِهِ، وَكُلُّ مَنِ اعْتَصَمَ بِهِ يَنْجُو.