መዝሙር 3 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 3:1-8

መዝሙር 3

የመከራ ተቀባዩ የጧት ጸሎት

ዳዊት ከልጁ ከአቤሴሎም በሸሸ ጊዜ የዘመረው መዝሙር።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ ጠላቶቼ ምንኛ በዙ!

ስንቱስ በእኔ ላይ ተነሣ!

2ብዙዎች ነፍሴን፣ “እግዚአብሔር

አይታደግሽም” አሏት። ሴላ3፥2 በመዝሙረ ዳዊት ውስጥ በተደጋጋሚ የሚገኝ ሲሆን፣ የቃሉ ትርጕም በትክክል አይታወቅም፤ የሙዚቃ ምልክት ሳይሆን አይቀርም

3እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ግን ዙሪያዬን

የምትከልል ጋሻ ነህ፤

ክብሬንና ራሴንም ቀና ቀና

የምታደርግ አንተ ነህ።3፥3 ወይም እግዚአብሔር… ወደ ላይ የምታነሣ ክብሬ ሆይ

4ወደ እግዚአብሔር ድምፄን ከፍ አድርጌ እጮሃለሁ፤

እርሱም ከተቀደሰ ተራራው ይመልስልኛል። ሴላ

5እተኛለሁ፤ አንቀላፋለሁ፤

እግዚአብሔር ደግፎ ይዞኛልና እነቃለሁ።

6በየአቅጣጫው የከበበኝን፣

አእላፍ ሕዝብ አልፈራም።

7እግዚአብሔር ሆይ ተነሥ!

አምላኬ ሆይ፤ ታደገኝ፤

የጠላቶቼን ሁሉ መንጋጋ ትመታለህ፤

የክፉዎችንም ጥርስ ትሰባብራለህ።

8ማዳን የእግዚአብሔር ነው፤

በረከትህ በሕዝብህ ላይ ይሁን። ሴላ

Thai New Contemporary Bible

สดุดี 3:1-8

สดุดี 3

(บทสดุดีของดาวิด เมื่อหนีจากอับซาโลมราชโอรส)

1ข้าแต่องค์พระผู้เป็นเจ้า ศัตรูของข้าพระองค์มีมากเหลือเกิน!

ผู้ที่ลุกขึ้นต่อต้านข้าพระองค์ก็มีมากมายนัก!

2หลายคนกล่าวถึงข้าพระองค์ว่า

“พระเจ้าจะไม่ทรงช่วยกู้เขา”

เสลาห์3:2 อ่านว่า เส-ลา ในภาษาฮีบรูคำนี้มีความหมายไม่ชัดเจน อาจจะเป็นศัพท์ทางดนตรี ปรากฏบ่อยๆ ในพระธรรมสดุดี

3ข้าแต่องค์พระผู้เป็นเจ้า แต่พระองค์ทรงเป็นโล่ล้อมข้าพระองค์ไว้

องค์ผู้ทรงเกียรติสิริของข้าพระองค์ ผู้ทรงเชิดชูข้าพระองค์ไว้ 4ข้าพเจ้าร้องทูลต่อองค์พระผู้เป็นเจ้า

และพระองค์ทรงตอบข้าพเจ้าจากภูเขาอันศักดิ์สิทธิ์ของพระองค์

เสลาห์

5ข้าพเจ้าเอนกายลงและหลับไป

ข้าพเจ้าตื่นขึ้นอีกเพราะองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงค้ำจุนข้าพเจ้า

6ข้าพเจ้าจะไม่กลัวศัตรูนับหมื่น

ที่รุมล้อมข้าพเจ้าอยู่รอบด้าน

7ข้าแต่องค์พระผู้เป็นเจ้า โปรดทรงลุกขึ้น!

ข้าแต่พระเจ้าของข้าพระองค์! โปรดทรงช่วยกู้ข้าพระองค์

ขอทรงตบหน้าศัตรูทุกคนของข้าพระองค์

ขอทรงเลาะฟันของเหล่าคนชั่ว

8การช่วยกู้มาจากองค์พระผู้เป็นเจ้า

ขอพระพรของพระองค์มีแก่เหล่าประชากรของพระองค์เถิด

เสลาห์