መዝሙር 27 – NASV & NIVUK

New Amharic Standard Version

መዝሙር 27:1-14

መዝሙር 27

ከእግዚአብሔር ጋር ያለው ሰው ድፍረት

የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔር ብርሃኔና መድኅኔ ነው፤

የሚያስፈራኝ ማን ነው?

እግዚአብሔር ለሕይወቴ ዐምባዋ ነው፤

ማንን እፈራለሁ?

2ሥጋዬን ይበሉ ዘንድ፣27፥2 ወይም ስሜን ሊያጠፉ

ክፉዎች ገፍተው በመጡ ጊዜ፣

ጠላቶቼና ባላጋራዎቼ በተነሡብኝ ጊዜ፣

እነርሱ ተሰነካክለው ወደቁ።

3ሰራዊት ቢከብበኝ እንኳ፣

ልቤ አይፈራም፤

ጦርነት ቢነሣብኝ እንኳ፣

ልበ ሙሉ ነኝ።

4እግዚአብሔርን አንዲት ነገር እለምነዋለሁ፤

እርሷንም እሻለሁ፤

ይኸውም በሕይወቴ ዘመን ሁሉ፣

በእግዚአብሔር ቤት እኖር ዘንድ፣

የእግዚአብሔርን ክብር ውበት አይ ዘንድ፣

በመቅደሱም ሆኜ አሰላስል ዘንድ ነው።

5በመከራ ቀን፣

በድንኳኑ ውስጥ ይሰውረኛልና፤

በድንኳኑም ጓዳ ይሸሽገኛል።

6በዚህ ጊዜ በዙሪያዬ ባሉ ጠላቶቼ ላይ፣

ራሴ ከፍ ከፍ ይላል፤

በድንኳኑም ውስጥ የእልልታ መሥዋዕት እሠዋለሁ፤

ለእግዚአብሔር እቀኛለሁ፤

እዘምርለታለሁም።

7እግዚአብሔር ሆይ፤ ድምፄን ከፍ አድርጌ ስጮኽ ስማኝ፤

ራራልኝ፤ ስማኝም።

8“ፊቴን ፈልጉ” ባልህ ጊዜ፤27፥8 ወይም ልቤ ሆይ፤ ለአንተ “ፊቴን” አለ

ልቤ፣ እግዚአብሔር ሆይ፤ ፊትህን እሻለሁ አለች።

9ፊትህን ከእኔ አትሰውር፤

ተቈጥተህ አገልጋይህን አታርቀው፤

መቼም ረዳቴ ነህና።

አዳኝ አምላኬ ሆይ፤

አትጣለኝ፤ አትተወኝም።

10አባቴና እናቴ ቢተዉኝ እንኳ፣

እግዚአብሔር ይቀበለኛል።

11እግዚአብሔር ሆይ፤ መንገድህን አስተምረኝ፤

ስለ ጠላቶቼም፣

በቀና መንገድ ምራኝ።

12ለጠላቶቼ ፍላጎት አሳልፈህ አትስጠኝ፤

የሐሰት ምስክሮች ተነሥተውብኛልና፣

ዐመፃ የሚረጩ ናቸው።

13የእግዚአብሔርን ቸርነት

በሕያዋን ምድር እንደማይ

ሙሉ እምነቴ ነው።

14እግዚአብሔርን ተስፋ አድርግ፤

አይዞህ፣ በርታ፤

እግዚአብሔርን ተስፋ አድርግ።

New International Version – UK

Psalms 27:1-14

Psalm 27

Of David.

1The Lord is my light and my salvation –

whom shall I fear?

The Lord is the stronghold of my life –

of whom shall I be afraid?

2When the wicked advance against me

to devour27:2 Or slander me,

it is my enemies and my foes

who will stumble and fall.

3Though an army besiege me,

my heart will not fear;

though war break out against me,

even then I will be confident.

4One thing I ask from the Lord,

this only do I seek:

that I may dwell in the house of the Lord

all the days of my life,

to gaze on the beauty of the Lord

and to seek him in his temple.

5For in the day of trouble

he will keep me safe in his dwelling;

he will hide me in the shelter of his sacred tent

and set me high upon a rock.

6Then my head will be exalted

above the enemies who surround me;

at his sacred tent I will sacrifice with shouts of joy;

I will sing and make music to the Lord.

7Hear my voice when I call, Lord;

be merciful to me and answer me.

8My heart says of you, ‘Seek his face!’

Your face, Lord, I will seek.

9Do not hide your face from me,

do not turn your servant away in anger;

you have been my helper.

Do not reject me or forsake me,

God my Saviour.

10Though my father and mother forsake me,

the Lord will receive me.

11Teach me your way, Lord;

lead me in a straight path

because of my oppressors.

12Do not hand me over to the desire of my foes,

for false witnesses rise up against me,

spouting malicious accusations.

13I remain confident of this:

I will see the goodness of the Lord

in the land of the living.

14Wait for the Lord;

be strong and take heart

and wait for the Lord.