መዝሙር 25 – NASV & NIVUK

New Amharic Standard Version

መዝሙር 25:1-22

መዝሙር 2525 ይህ መዝሙር እያንዳንዱ ጥቅስ ተከታታይ ፊደላት ባሉት የዕብራይስጥ ሆህያት የሚጀምር፣ ጅማሬው ወይም ጅማሬውና መጨረሻው ትርጕም የሚሰጥ ግጥም ነው።

በዐደጋ ጊዜ የቀረበ ጸሎት

የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔር አምላክ ሆይ፤ ነፍሴን ወደ አንተ አነሣለሁ፤

2አምላኬ ሆይ፣ በአንተ እታመናለሁ፤

እባክህ አታሳፍረኝ፤

ጠላቶቼም አይዘባነኑብኝ።

3አንተን ተስፋ የሚያደርጉ፣

ከቶ አያፍሩም፤

ነገር ግን እንዲያው ያለ ምክንያት፣

ተንኰለኞች የሆኑ ያፍራሉ።

4እግዚአብሔር ሆይ፤ አካሄድህን እንዳውቅ አድርገኝ፤

መንገድህንም አስተምረኝ።

5አንተ አዳኜ፣ አምላኬም ነህና፣

በእውነትህ ምራኝ፤ አስተምረኝም፤

ቀኑን ሙሉ አንተን ተስፋ አድርጌአለሁ።

6እግዚአብሔር ሆይ፤ ምሕረትህንና ፍቅርህን ዐስብ፤

እነዚህ ከጥንት የነበሩ ናቸውና።

7የልጅነቴን ኀጢአት፣

መተላለፌንም አታስብብኝ፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ እንደ ቸርነትህ ብዛት፣

እንደ ምሕረትህም መጠን አስበኝ።

8እግዚአብሔር መልካምና ቅን ነው፤

ስለዚህ ኀጢአተኞችን በመንገድ ይመራቸዋል።

9ዝቅ ያሉትን በፍትሕ ይመራቸዋል፤

ለትሑታንም መንገዱን ያስተምራቸዋል።

10ኪዳኑንና ሥርዐቱን ለሚጠብቁ፣

የእግዚአብሔር መንገድ ሁሉ ቸርነትና እውነት ናቸው።

11እግዚአብሔር ሆይ፤ ኀጢአቴ ታላቅ ነውና፣

ስለ ስምህ ይቅር በልልኝ።

12እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰው ማን ነው?

በተመረጠለት መንገድ ያስተምረዋል።

13ዘመኑን በተድላ ደስታ ያሳልፋል፤

ዘሩም ምድርን ይወርሳል።

14እግዚአብሔር ምስጢሩን ከሚፈሩት ወዳጆቹ አይሰውርም፤

ኪዳኑንም ይገልጥላቸዋል።

15ዐይኖቼ ሁልጊዜ ወደ እግዚአብሔር ናቸው፤

እግሮቼን ከወጥመድ የሚያላቅቃቸው እርሱ ነውና።

16እኔ ብቸኛና የተጨነቅሁ እንደ መሆኔ፣

ወደ እኔ ተመለስ፤ ምሕረትም አድርግልኝ።

17የልቤ መከራ በዝቷል፤

ከጭንቀቴ ገላግለኝ።

18ጭንቀቴንና መከራዬን ተመልከት፤

ኀጢአቴንም ሁሉ ይቅር በለኝ።

19ጠላቶቼ እንዴት እንደ በዙ ተመልከት፤

እንዴት አምርረው እንደሚጠሉኝ እይ።

20ነፍሴን ጠብቃት፤ ታደገኝም፤

መጠጊያዬ ነህና አታሳፍረኝ።

21አንተን ተስፋ አድርጌአለሁና፣

ታማኝነትና ቅንነት ይጠብቁኝ።

22አምላክ ሆይ፤ እስራኤልን

ከመከራው ሁሉ አድነው።

New International Version – UK

Psalms 25:1-22

Psalm 25This psalm is an acrostic poem, the verses of which begin with the successive letters of the Hebrew alphabet.

Of David.

1In you, Lord my God,

I put my trust.

2I trust in you;

do not let me be put to shame,

nor let my enemies triumph over me.

3No-one who hopes in you

will ever be put to shame,

but shame will come on those

who are treacherous without cause.

4Show me your ways, Lord,

teach me your paths.

5Guide me in your truth and teach me,

for you are God my Saviour,

and my hope is in you all day long.

6Remember, Lord, your great mercy and love,

for they are from of old.

7Do not remember the sins of my youth

and my rebellious ways;

according to your love remember me,

for you, Lord, are good.

8Good and upright is the Lord;

therefore he instructs sinners in his ways.

9He guides the humble in what is right

and teaches them his way.

10All the ways of the Lord are loving and faithful

towards those who keep the demands of his covenant.

11For the sake of your name, Lord,

forgive my iniquity, though it is great.

12Who, then, are those who fear the Lord?

He will instruct them in the ways they should choose.25:12 Or ways he chooses

13They will spend their days in prosperity,

and their descendants will inherit the land.

14The Lord confides in those who fear him;

he makes his covenant known to them.

15My eyes are ever on the Lord,

for only he will release my feet from the snare.

16Turn to me and be gracious to me,

for I am lonely and afflicted.

17Relieve the troubles of my heart

and free me from my anguish.

18Look on my affliction and my distress

and take away all my sins.

19See how numerous are my enemies

and how fiercely they hate me!

20Guard my life and rescue me;

do not let me be put to shame,

for I take refuge in you.

21May integrity and uprightness protect me,

because my hope, Lord,25:21 Septuagint; Hebrew does not have Lord. is in you.

22Deliver Israel, O God,

from all their troubles!